01/14/2026
ከአይሾው ስፒድ የኢትዮጲያ ጉብኝት የተረዳናቸው እውነታዎች።
አንድ፦ ቋንቋ ወሳኝ መሆኑን
እንሊዘኛ እውቀት አይደለም፣ እንግሊዘኛ አይበላ የሚሉትን ትታችሁ ቋንቋ ወንዝ ያሻግራል የሚለውን ያዙ።እድል እብድ ነው መቼ እንደሚመጣ አይታወቅም እና ተዘጋጅታችሁ ጠብቁ።የተዘጋጁ ሲያንበለብሉት አይተናል ፤ ራስን መግለፅ እና መግባባት መቻል ትልቅ ሳሪያ ነው፤ ብዙ ትርፍ አለው።
ሁለት ፦የኮሪደር ልማት
ከቤት ወደ ከተማ ወይ ከከተማ ወደ ቤት ይሁን የሚለው የስትራቴጂ ጉዳይ ቢሆንም ፤ የኮሪደር ልማቱ ምርጥ መሆኑን አይተናል፤ አዲስ አበባ አምሮባታል ብዙዎች ስለሀገራችን ያላቸው እይታ ይቀየራል # National branding ፤ ከሞላ ጎደል መንግስታችን የዲጂታል ዲፕሎማሲ እና ኢኮኖሚ እድሉን ጥሩ ተጠቅሞበታል።
ሶስት ፦የአንድ ሰው አቅም
የሶሻል ሚዲያ ገለል የምናደርገው ነገር እንዳልሆነ ፤ አቅም እንዳለው አሳይቶናል፤የነጠላ ሰው አቅም (One man media) አለምን ማነቃነቅ እንደሚሚችል አሳይቶናል።