03/01/2026
"2 በር - በ 1 ቁልፍ" ቴምር ፕሮፐርቲስ
| ቴምር ፕሮፐርቲስ ለደንበኞቹ ያዘጋጀው የመኪና ሽልማት አበረከተ።
"2 በር - በ 1 ቁልፍ" በሚል መሪ ቃል የቴምር ስጦታ ኤክስፖ ዝግጅት በዛሬው እለት በታላቅ ድምቀት ተከፍቷል።
ኤክስፖው ከዛሬ ቅዳሜ ታህሳስ 25/2018 እስከ ከታህሳስ 27/2018 ድረስ ይቆያል ተብሏል።
ቴምር ፕሮፐርቲ ከብሔራዊ ሎተሪ የመጡ ባለሙያዎች በተገኙበት ለደምበኞቹ 2 BYD መኪኖችን እንዲሁም 4 የእለቱ እድለኞች ደግሞ ለእያንዳንዳቸው የአንድ ሚሊየን ብር ለቤት ግንባታ ማጠናቀቂያ የሚሆን ገንዘብ ሽልሟል።
ቴምር፦
የቤት አልሚ ብቻ አለመሆኑ ተገልጾ ምርጥ ኢትዮጵያውያን መሐንዲሶችና ባለሙያዎችም የሚፈሩበት፣ የጥራት ደረጃ የሚቀመርበት የልህቀት ማዕከል መሆኑን ተገልፀዋል።
ከ10 አመት በፊት 50 ሰራተኞችን ብቻ ይዞ ስራ የጀመረው ቴምር ፕሮፐርቲስ በ2026 የሰራተኞቹን ቁጥር 1ሺህ ለማድርስ ይዞት የነበረውን እቅድ ቀደም በሎ ማሳካት እንደቻለም ገልፀዋል።
10ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በተለያዩ ደማቅ ሁነቶች ለማክበር በዝግጅት ላይ እንደሚንኝም ተገልጿል።
ቴምር ፕሮፐርቲስ በሁለት ባስራዕዮች በ2008 ዓ.ም ሲመሰረት፣ ዓላማው ቤት መገንባት ብቻ ሳይሆን የሪል ስቴት ዘርፋን በግንባታ፣ በገበያ አመራር ፣ በደንበኛ አያያዝ በቴክኖሎጂ እና በሌሎችም ዘርፎች አንድ እርምጃ የማሻገር አላማ ይዞ እየሰራ ይገኛል ተቅሏል።