Jabaan Waaqa ጀባን ዋቃ

Jabaan Waaqa ጀባን ዋቃ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Jabaan Waaqa ጀባን ዋቃ, Real Estate, Addis Ababa.

08/02/2023
08/02/2023

ዲፕሎማሲያችን ወደፊት‼️

በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የተመራው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን በአውሮፓ ዲፕሎማሲያዊ ጉብኝቶችን ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል ሀገራቱም ጣልያን ፈረንሳይ ማልታ ሲሆኑ በንግድ፣ ኢንቨስትመንት፣ ቱሪዝም፣ በባሕር፣ በሎጅስቲክስ እና በጸጥታ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ከማልታ ጋር የተስማሙ ሲሆን እንዲሁም በጣሊያን በኩል 180 ሚሊዮን ዩሮ እርዳታ እና ለስላሳ ብድርን የሚያካትት የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት በመፈራረም ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም እና የአስር ዓመት የልማት እቅዶችን ለማስቀጠል የሚደግፍ ስምምነት ላይ መድረስ የተቻለ ሲሆን .....

እንዲሁም በፈረንሳይ በኩል ደግሞ በተጠናከረ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና የፈረንሳይ የግሉ ዘርፍ ኢትዮጵያ ቅድሚያ በምትሰጣቸው ዘርፎች ላይ መሳተፍ እንዲችሉ ተወያይተዋል።

ከውይይቱ ጎን ለጎን በዲፕሎማሲው ዘርፍ ሀገራችን በአውሮፓ ያላትን ተጠቃሚነትና በአካባቢው የሚኖራትን ተደማጭነት ከፍ የሚያደርግ ስራ እየተሰራ ለመሆኑ ማረጋገጫ ነው! ይህም ሀገራችን የያዘችውን የልማት መንገድ በመደገፍ አንድ እርምጃ መራመድ እንድንችል የሚያደርግ ሊጎለብት የሚገባው አመርቂ ስራ ነው ።

08/02/2023

"ኢትዮጵያውያን አንዳቸው ለአንዳቸው ጋሻና መከታ ሆነው በትብብር መስራት ከቻሉ፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ በብዙ ነገር ሻል ያለች ሀገር ማድረግ እንደሚቻል ምንም ጥርጥር የለውም።"

- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)

08/02/2023

ከፀጥታና ደኅነት የጋራ ግብረ–ኃይል ወቅታዊ የጸጥታ ጉዳይን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ ፦

ሰሞኑን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የተከሰተውን ወቅታዊ ሁኔታ የገመገመው የፀጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አለመግባባቱን ለመፍታት የሚደረገው ጥረት በሰላማዊ መንገድ ብቻ እንደሚፈጸም የጸና እምነት አለው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የጋራ ግብረኃይሉ በተለያዩ ሚዲያዎች ከሚሰራጩ ዘገባዎችና በመረጃ ስምሪቱ ባሰባሰባቸው ግብዓቶች መሠረት በእምነቱ አባቶች በተመሳሳይ ቀንና ቦታ ሕገወጥ የሰልፍ ጥሪ በማድረግ የዜጎች ህይወት የሚቀጠፍበት አጋጣሚ እንዲፈጠር ቅስቀሳዎች እየተደረጉና ሌሎችም ግጭት ቀስቃሽተግባራት እየተፈፀሙ መሆኑን ማረጋገጥ ችሏል።

ይህ አካሄድ ክስተቱን እንደ ሽፋን በመጠቀም ከውስጥና ከውጭ ተቀናጅተው ሀገራችንን ለማፍረስለሚሰሩ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በር እየከፈተ መሆኑን መላው የሀገራችን ሕዝብና የዕምነቱ ተከታዮች ግንዛቤ ሊወስዱ እንደሚገባ የጋራ ግብረ-ኃይሉ አመልክቷል።

ትናንት ታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በሀገራችን እንገነባለን ስንል “እኛ ካልፈቀድንላችሁ በስተቀርመገንባት አትችሉም” ሲሉን የነበሩ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ዛሬ በውስጥ ጉዳያችን ጣልቃ በመግባት አለመግባባቱን ለማባባስ ጊዜ አልወሰደባቸውም ያለው የጋራ ግብረ–ኃይሉ÷ እነዚህ የውጭ አካላት በቅርቡበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የተፈጠረውን አለመግባባት እንደ እድል በመጠቀምልዩነትን የሚያጎላ እና ችግሩን የሚያባብስ እንቅስቃሴ ውስጥ መገኘታቸውን የተገኘው መረጃ ጠቁሟል።

ስለሆነም መላው የሀገራችን ሕዝብ፣ የዕምነቱ አባቶችና የዕምነቱ ተከታዮች ታሪካዊ ጠላቶቻችን ከውስጥየሽብር ኃይሎች ጋር እንዲሁም በማኅበራዊ ሚዲያ አንቂ ስም ከሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች አና በአቋራጭስልጣን ለመያዝ ከሚሹ አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተቀናጅተው ሀገራችንን ወደማያባራ ብጥብጥ ለማስገባት እያደረጉ ያሉትን ቅስቀሳና እንቅስቃሴ በውል ተገንዝባችሁ የእኩይ ዓላማቸው ማስፈፀሚያእንዳትሆኑ የጋራ ግብረ-ኃይሉ በአጽንኦት አሳስቧል።

በሃይማኖቱ ሽፋን የሚደረጉ የሕገወጥ ሰልፎቹ ቅስቀሳዎች የተለያዩ የሚዲያ አውታሮችን በመጠቀምናበህቡዕ በመደራጀት የአፍሪካ ሕብረትን ዓመታዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ ለማካሄድ ዝግጅት እየተጠናቀቀ ከሚገኝበት ወቅት ጋር እንዲገጣጠሙ በማድረግ በሀገሪቱ የደኅንነት ስጋት እንዳለ በማስመሰል ጉባኤውእንዲስተጓጎል ሆን ተብሎ በዕቅድ እየተመራ መሆኑን የፀጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ–ኃይሉ ደርሶበታል።

ሕገወጥ እንቅስቃሴዎቹ ደም አፋሳሽ እንዲሆኑ ታቅዶ ችግሩ ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ አካባቢዎችበርካታ የጦር መሣሪያዎች ሲዘዋወሩ የነበሩ ሲሆን÷ ግብረ –ኃይሉ ባካሄደው የተቀናጀ ኦፕሬሸን ከአዘዋዋሪ የደም ነጋዴ እንዲሁም ሽብርተኞች ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ይገልፃል።

በመሆኑም በዚህ ጉዳይ ላይ በሚመለከተው አካል የተፈቀደ ሰልፍ የሌለ መሆኑ ታውቆ ኅብረተስቡ ከዚህሕገ ወጥ ሰልፍና ግጭት ቀስቃሽ ተግባራት ራሱን እንዲጠብቅ የጋራ ግብረ–ኃይሉ ያስጠነቀቀ ሲሆን÷ መላው ሕዝብ፣ የዕምነቱ አባቶችና ተከታዮች ለሀገራችን ሰላምና ደኅንነት እንደወትሮ ዘብ በመቆም ከፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረኃይል ጋር ተቀናጅታችሁ እንድትሠሩ እና ማንኛውም አለመግባባት በሠላማዊ መንገድ ብቻ እንዲፈታ የበኩላችሁን እንድትወጡ ጥሪውን ያቀርባል።

የጋራ ግብረ-ኃይሉ ከዚህ ውጭ ሰልፍ አደርጋለሁ ብሎ በሕገ ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀስ ማንኛውም ኃይል እንዲሁም ሰልፎቹን ለማስተባበር እና ለመሳተፍ የሚሞክሩ አካላት ለሚደርሰው ማንኛውም ጉዳት ተጠያቂ መሆናቸውን በማሳሳብ ግብረ – ኃይሉ ለዜጎችና ለሀገር ሰላምና ደኅንነት መረጋገጥ ሲባል ሕጋዊእርምጃ እንደሚወስድ ከወዲሁ በጥብቅ ያሳውቃል።

የጋራ ግብረ-ኃይሉ ለቤተክርስቲያኗ አባቶች እና ለዕምነቱ ተከታዮች የሚደረገውን የደኅንነት ጥበቃ ለማጠናከር በሚያስችል መልኩ እንደሚቀጥል ጠቁሟል፡፡

በየክልሉ የምትገኙ የፀጥታ ኃይሎችም በአካባቢያችሁ ሕገወጥ ሰልፎች እንዳይካሄዱ አስፈላጊውን ክትትልና ቁጥጥር እንዲሁም ለቤተ ክርስቲያኗ፣ ለእምነቱ አባቶች እና ተከታዮች በአጠቃላይ ለሕዝቡ ተገቢውን የደኅንነት ጥበቃ እንድታደርጉ የጋራ ግብረ –ኃይሉ ያሳስባል።

በመጨረሻም ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ፀረ-ሰላም ኃይሎች የሀገራችንን ስላምና ደኅንነት ለማደፍረስ ዝግጅት ማድረግ በመጀመራቸው ኅብረተሰቡ እንደተለመደው ሁሉ አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ በማድረግ አካባቢውን በንቃት በመጠበቅ ከግብረ -ኃይሉ ጎን እንዲቆም በድጋሚ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረኃይል ጥሪውን ያቀርባል።

የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረኃይል
የካቲት 1 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

05/02/2023

ሰላም ለኢትዮጵያ ይሁን ፤
ፍቅር እና አንድነት ለኢትዮጵያ ይሁን ፤
መተሳሰብ ለኢትዮጵያ ይሁን ፤
መበልጸግ ለኢትዮጵያ ይሁን ፤
መርዳት ለኢትዮጵያ ይሁን ፤
የኛ መሻት እና ፍላጎት ይኼ ነው።

- ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

05/02/2023

በወቅታዊ ጉዳይ ከመንግሥት ኮሙኒኬሽን የተሰጠ መግለጫ

ከሰሞኑ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል የተፈጠረው መለያየት ሰላማዊ በሆነ መንገድ፣ በውስጣዊ አሠራር መፈታት እንዳለበት መንግሥት ያምናል።

ሀገራዊ ተቋማት አንድነታቸውንና ጥንካሬያቸውን ጠብቀው እንዲዘልቁ ከዚህ በፊትም ሆነ ችግሮች በተፈጠሩ ጊዜ ሁሉ መንግሥት የሚጠበቅበትን ሲወጣ ቆይቷል። ይሄንን ጥረቱን አሁንም አጠናክሮ ይቀጥላል። የተቋማቱን አንድነት የሚፈታተኑ ችግሮች ከውስጥ ሲነሡ በውይይትና በውስጣዊ አሠራር እንዲፈቱ ድጋፍ ሲያደርግ ነበር። በተጨባጭም ውጤት አምጥቷል።

ከሰሞኑ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች መካከል የተፈጠረው መለያየት በሰላማዊ መንገድ በውይይትና በቤተ ክርስቲያኒቱ አሠራር መሠረት እንዲፈታ ሁሉም አካላት የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት መወጣት ይኖርባቸዋል። የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ሁለቱን ወገኖች በማቀራረብ ችግሩ በሰከነ መንገድ እንዲፈታ ማድረግ አለባቸው።

አማኞች ችግሩን ከማወሳሰብና ለሌሎች አካላት መጠቀሚያ ከመሆን በመታቀብ ገንቢ ሚና ሊጫወቱ ይገባል። የጸጥታ አካላት የየአካባቢውን ሕዝብና የእምነት ተቋማት ሰላምና ጸጥታ ማስከበር ግዴታቸው ነው። ግጭት የሚያባብሱ አካላትንም ሥርዓት ማስያዝ አለባቸው። የሚዲያ አካላት ችግሩን የሚያባብሱ ነገሮችን ከማቅረብ መቆጠብ ይጠበቅባቸዋል። እንዲሁም መላው ሕዝብ ለችግሩ መፈታት የሚጠበቅበትን እንዲያደርግ መንግሥት ያሳስባል።

በሌላ በኩል እምነትና ብሔርን ተገን አድርገው ግጭት ለመፍጠር የሚያስቡ፣ ሀገር ለማፍረስ በተለያዩ መንገዶች ሞክረው ያልተሳካላቸው ኃይሎች፣ ችግሩ እንዲባባስና እንዳይፈታ ለማድረግ እየሠሩ መሆኑ ተደርሶበታል። መንግሥት ይሄንን ፈጽሞ አይታገሥም።

ችግሩን ለማባባስና በሕዝቦች መካከል ግጭት ለመፍጠር፣ ብሎም ሀገርን ወደፈተና ለማስገባት በሚጥሩ አካላት ላይ መንግሥት ሕግ የማስከበር ሥራውን እንደሚሠራ በዚሁ አጋጣሚ ያሳውቃል።

ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

03/02/2023

Address

Addis Ababa
1919

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jabaan Waaqa ጀባን ዋቃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Jabaan Waaqa ጀባን ዋቃ:

Share

Category