Selam Tesfaye Ejigu Advertising & Commission Enterprize

Selam Tesfaye Ejigu Advertising & Commission Enterprize Bahiran Media and Marketing

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት የክብር ዶ/ር ...
19/10/2025

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የነበሩት የክብር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል፡፡

ባህራን ሚዲያና ማርኬቲንግ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ መጽናናትን ይመኛል፡፡

ኢትዮጵያ የግብፅን ውንጀላ መሠረተ ቢስ ነው ስትል አጣጣለች   | ለሱዳን ጎርፍ ኢትዮጵያን ተጠያቂ ያደረገው የግብፅን ውንጀላ፣ "ዓለም አቀፉን ማሕበረሰብ ለማሳሳት የቀረበ    መሠረተ ቢስ ...
04/10/2025

ኢትዮጵያ የግብፅን ውንጀላ መሠረተ ቢስ ነው ስትል አጣጣለች

| ለሱዳን ጎርፍ ኢትዮጵያን ተጠያቂ ያደረገው የግብፅን ውንጀላ፣ "ዓለም አቀፉን ማሕበረሰብ ለማሳሳት የቀረበ መሠረተ ቢስ ክስ ነው" ስትል ኢትዮጵያ አጣጥላለች፡፡

የግብፅ የውሃ ሀብትና መስኖ ሚኒስቴር ውንጀላ መሠረተ ቢስ ነው ያለው የኢትዮጵያ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር መግለጫ፤ ከህዳሴ ግድብ ግንባታ በፊት ያሉና አሁናዊ መረጃዎችን በማስረጃነት አቅርቧል።

ከህዳሴ ግድበ ግንባታ በፊት የነበረው የጎርፍ መጠን በነሐሴ ወራት በቀን ከ800 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ፣
በመስከረም ወራት በቀን ከ750 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ ይደርስ እንደነበር ሚኒስቴሩ ጠቁሟል፡፡

ከግድቡ ግንባታ በኋላ የጎርፍ መጠኑ በነሐሴ 2025 ዕለታዊ የውሃ መጠን 154.7 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ሲሆን፤ በመስከረም 2025 472 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ እንደነበር ጠቅሷል።

"የሕዳሴ ግድብ በላይኛው ተፋሰስ ሀገራት ከፍተኛ የዝናብ ወቅት የተለመደ የነበረውን አውዳሚ ጎርፍ በመቆጣጠር የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ማሕበረሰቦችን ህይወትና ንብረት ይጠብቃል።

ሕዳሴ ግድብ ባይኖር ኖሮ ባለፉት ጥቂት ወራት በኢትዮጵያ ደጋማ አካባቢዎች የተስተዋለው ከባድ ዝናብ፣ በሱዳንና በግብፅ የሰው ሕይወትና የመሠረተ ልማት አውታሮች ላይ ታሪካዊ ውድመት ሊያስከትል ይችል ነበር፡፡" ሲል የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር በመግለጫው አስረድቷል፡፡

የሱዳን የግብርና እና መስኖ ሚኒስቴር በሀገሪቱ የተከሰተው ጎርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌለው ማንሳቱን የጠቀሰው መግለጫው፤ ግብጽ በተቃርኖ በመቆም ዓለም አቀፉን ማሕበረሰብ ለማሳሳት ሀሰተኛ ክስ አቅርባለች ብሏል፡፡

ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሱዳን ጋር የመረጃ ልውውጥና ትብብር ማዕቀፍን በማቋቋም አውዳሚ የጎርፍ መጠንን በመቀነስ፣ ግድቡ ለሱዳን በረከት ሆኖ እንዲቀጥል ከሚመለከታቸው የሱዳን ባለሥልጣናትና ባለሙያዎች ጋር በቅርበት መሥራቷን እንደምትቀጥል ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስታውቋል።

6 ዓመታት ሞላው...ለታላቁ የጥበብ ሰው ኤልያሳ መልካን መታሰቢያበዚች ዕለት፣ በዚች ሰዓት... 💔የታላቁ የጥበብ ሰው ኤልያሳ መልካን ከዚህ ዓለም በሞት ከተለየ 6 ዓመታት ሞሉን።አንተ ታላቅ...
04/10/2025

6 ዓመታት ሞላው...

ለታላቁ የጥበብ ሰው ኤልያሳ መልካን መታሰቢያ
በዚች ዕለት፣ በዚች ሰዓት... 💔

የታላቁ የጥበብ ሰው ኤልያሳ መልካን ከዚህ ዓለም በሞት ከተለየ 6 ዓመታት ሞሉን።

አንተ ታላቅ "ኤሉ" ሆይ፣ የእውቀትህና የጥበብህ ውርስ ለዘላለም ይኖራል።

ካጣንህ ጊዜ ጀምሮ ልባችን ናፍቆሃል፣ ግን በአንተ አስደናቂ ስራዎችና አስተዋጽዖዎች ውስጥ ሁሌም ህያው ሆነህ ትኖራለህ።

የናፈቅነው ታላቅ ሰው፣
ሁሌም በልባችን ትኖራለህ!

🙏🏾🙏🏾🙏🏾

" ማንኛውንም ጫና ተቋቁማችሁ ለሰራተኛው ከዚህ ወር ጀምሮ አዲሱን የመግስት ሰራተኞች ደሞዝ መክፈል አለባችው።  " - ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የፊዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መ...
03/10/2025

" ማንኛውንም ጫና ተቋቁማችሁ ለሰራተኛው ከዚህ ወር ጀምሮ አዲሱን የመግስት ሰራተኞች ደሞዝ መክፈል አለባችው። " -
ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን

የፊዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ ለሁሉም ክልሎችና ለሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊዎች እና ለሚመለከታቸው አካላት በአዲሱ የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ጭማሪና የአበል ክፍያ በሚመለከት መመሪያ አስተላልፈዋል።

በሰጡት መመሪያ መሰረትም ከመስከረም ወር ጀምሮ አዲሱ የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ተግባራዊ እንደሚሆን አሳውቀዋል።

ኮሚሽነሩ " የደሞዝና የአበል ማስተካከያ የተደረገው መንግስት የመክፈል አቅም ኖሮት ሳይሆን የመንግስት ሰራተኛውን የኑሮ ጫና ስለሚያውቅ ትልቅ ዋጋ ተከፍሎ ነው " ብለዋል።

" ይህም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) የተወሰደ ትልቅ እርምጃ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ኮሚሽነሩ " ደሞዙ ከመስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ይከፈላል ክልሎች ምንአልባት አንዳንድ አካባቢዎች በዚህ ወር ካልደረሰ ያለውን ማንኛውንም ጫና ተቋቁማችሁ ለሰራተኛው ከዚህ ወር ጀምሮ አዲሱን የመግስት ሰራተኞች ደሞዝ መክፈል አለባቹ " ሲሉ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

28/05/2022
21/03/2022

MONDAY IS
A new start of your life
New beginning
New perspective
Make today count.
Have a great day!

Address

Addis Abeba
Addis Ababa
KAZANCHIS

Telephone

+251944275776

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Selam Tesfaye Ejigu Advertising & Commission Enterprize posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Selam Tesfaye Ejigu Advertising & Commission Enterprize:

Share