04/03/2026
እንኳን ደስ አላችሁ፤ አዲስ ምዕራፍ ጀምረናል።
አንጋፋው እና በመላው ኢትዮጵያውያን ዘንድ የተከበረው ጋዜጠኛ ደረጄ ኃይሌ የጃምቦ ሪል እስቴት የብራንድ አምባሳደር በመሆን በይፋ አጋራችን መሆኑን በታላቅ ኩራት እንገልጻለን።
በህዝብ ዘንድ ታማኝነትን ያተረፈው ተወዳጁ ደረጄ በደንበኞቹ ታማኝነትን ካተረፈው የብዙዎች ኩራት ከሆነው ጃምቦ ሪል ስቴት ጋር በመሆኑ ሰፋፊ የማስታወቂያ እና የኪነጥበብ ስራዎችን በጋራ የሚሰራ ይሆናል::
ይህ አጋርነት በገበያ ውስጥ ያለንን ተፅዕኖ ከማጠናከሩም በላይ ራዕያችንን በማስፋት፣ በታማኝነት፣ በጥራት እና በላቀ አገልግሎት ላይ የተመሰረቱ ግንባታዎችን ለማቅረብ ያለንን ቁርጠኝነት እንዲሁ ያረጋግጣል።
ለክቡራን ደንበኞቻችን እና የወደፊት የቤት ባለቤቶች፤ ወደ ጃምቦ ሪል እስቴት ቤተሰብ እንኳን በደህና መጣችሁ። ማህበራዊ ገፆቻችንን በመቀላቀል አብራችሁን ቆዩ::
እየገነባን ያለነው የወደፊት ተስፋ የሚጀምረው ከእናንተ ነው።