LECON Real Estate

LECON Real Estate Expecting More Than Others Think is Possible

11/09/2021
26/07/2020
29/06/2020
17/02/2020

ከለቡ-ጀሞ የብስክሌት ትራንስፖርት አገልግሎት ስራ ጀመረ

በአዲስ አበባ ከተማ ከለቡ ጀሞ የተሰራውን የሞተር አልባ ትራንፖርት አገልግሎት መስጫ መንገድ ስራ መጀመሩን የከተማዋ የትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።

የብስክሌት ትራንስፖርት አገልግሎት የጀመረው ነዋሪው ብስክሌትን እንደ አንድ የትራንስፖርት አማራጭ እንዲጠቀም ታስቦ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ስጦታው አካለ ተናግረዋል።

ለከተማዋ የሚመጥን የትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት የሚያስችሉ መሰረተ ልማቶችን በዓይነትና በብዛት ተደራሽ ማድረግም አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።

በመሆኑም በቅርቡ ከቃሊቲ- ቱሉ ዲምቱ 11 ኪሎ ሜትር መንገድ እና ከሃይሌ ጋርመንት- ጀሞ 4 ኪሎ ሜትር መንገድ ተመሳሳይ የብስክሌት ትራንስፖርት አገልግሎት ይጀመራል ብለዋል።

በዛሬው ዕለት ለምረቃ የበቃው ከለቡ-ጀሞ የተሰራው የብስክሌት ትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ መንገድ የ2 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ እንዳለው ነው የተነገረው።
ከዚህ ጎን ለጎን በከተማዋ “አብነት” እና “ስታዲየም” አካባቢዎች የብስክሌት መለማመጃ ቦታዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በመጪዎቹ 10 ዓመታት የ100 ኪሎ ሜትር የብስክሌት ትራንስፖርት መስመር ለመዘርጋት መታቀዱን ከቢሮው የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

የብስክሌት ትራንስፖርት አገልግሎት በሰዎች የአካል እንቅስቃሴ ማነስ ምክንያት ለሚመጣ የጤና ችግር፣ ወጪ ለመቀነስና የአየር ብክለትን ለመከላከል ጉልህ ፋይዳ አለው።

መንገዱ ለብስክሌት ተጠቃሚዎች ተደራሽ መደረጉ ለጤናማ እንቅስቃሴ፣ የመንገድ መዘጋጋትን ለመቀነስ፣ ለመዝናናት፣ የድምጽና የአየር ብክለትን ለመቀነስ ትልቅ እንደሚኖረው ተጠቁሟል።

ምንጭ፡- ኢዜአ

FYI
02/02/2020

FYI

የአዲስ አበባ ከተማን የጎንዮሽ መስፋፋት ለመግታት ያለመ አስገዳጅ የሕንፃዎች ከፍታ መጠን ሕግና አፈጻጸሙን የሚቆጣጠር ደንብ፣ የከተማዋ አስተዳደር ሊያወጣ መሆኑን ምንጮች ገለጹ፡፡

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00

Telephone

+251911250201

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when LECON Real Estate posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to LECON Real Estate:

Share

Category