28/07/2026
ሪች ላንድ ባዮኬሚካል ኢንዱስትሪ ከመደበኛ የኢንዱስትሪ ልማት ስራው በተጨማሪ ማህበራዊ ኃላፊነቱን/ Social Corporate Responsibility / ለመወጣት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ወገኖች ከ35 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ደረጃቸውን በጠበቀ ሁኔታ ያስገነባቸውን 20 የመኖሪያ ቤቶች ለቡሬ ከተማ አስተዳደር አስረከበ፡፡
በክልላችን በምዕ/ጎጃም ዞን በቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ የሚገኘው ሪች ላንድ ባዮኬሚካል ፕሮዳክሽን ፒ.ኤል.ሲ /Rich Land Biochemical Production PLC/ የተሰኘው ግዙፍ ካምፓኒ ከ35 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለ20 በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ወገኖች ያስገነባቸውን ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶች አጠናቅቆ በ18/11/2018 ዓ/ም ለከተማ አስተዳደሩ ርክክብ ፈፅሟል።
ድርጅቱ ከቡሬ ከተማ አስተዳደር በተሰጠው 2 ሺ 5 መቶ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ በሶስት ብሎኮች ያስገነባቸው ቤቶች በብሎኬት የተገነቡና የግንባታ ደረጃቸውን የጠበቁ ሲሆን 20 አባውራዎችንና እማውራዎችንም ተጠቃሚ የሚያደርጉ ናቸው።
በዚህ ሂደት እና ካምፓኒው በሚያከናውናቸው ሌሎች ሁለንተናዊ ተግባራቶች ላይም የአ/ብ/ክ/መ/ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና የቡሬ ኢንዱስትሪ ፓርክ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አጋርነት እና ሚና ከፍ ያለ አስተዋፆ የነበረው መሆኑ ተጠቃሽ ነው፡፡
የቡሬ ከተማ ነዋሪዎችም የፋብሪካውን መልካም አርዓያነት በማድነቅ፣ መሰል የማህበራዊ ኃላፊነት ተግባራት በሌሎች ባለሀብቶችም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
በዕለቱም የምዕራብ ጎጃም ዞን ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ አቶ አባይ አለሙ፣የቡሬ የተቀናጀ አግሮ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዳኛቸው አስረስ ፣ የምዕራብ ጎጃም ዞን ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ወይዘሮ ሸጋየ ያረጋል፣የቡሬ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀይማኖት አሰፋ፣የቡሬ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣የሀገር ሽማግሌዎች፣የሪች ላንድ ሰራተኞች በርክክቡ ተገኝተዋል::
ሪች ላንድ ባዮኬሚካል ፕሮዳክሽን ፒ.ኤል.ሲ /Rich Land Biochemical Production PLC/ ላደረገው በአርዓያነት የሚጠቀስ ተግባር የአ/ብ/ክ/መ/ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና የቡሬ ኢንዱስትሪ ፓርክ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ከፍ ያለ ምስጋና ለማቅረብ እንፈልጋለን፡፡
ዜጎችን ተደራሽ ያደረገ የማህበራዊ ሃላፊነትን / Social Corporate Responsibility / የመወጣት ጉዳይ የሁሉም የመንግስት እና የግል ባለሃብቱ ጥምር ሃላፊነት በመሆኑ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል፡፡