YH fuad

YH fuad Haramaya

20/08/2024
20/08/2024
24/04/2024
10/11/2022

!

ሰኞ ኅዳር 5/2015 ዓ.ም በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ስልጠና ማዕከል ውስጥ ይካሄዳልና እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል!
2፡30

09/10/2022

Hara melaal tube irra argatuu

26/08/2022

Itti An/pirasadantii Yuunivarsitii Haramaya Dr Hisaq Yusuf shanyii filaatama shunkurata qoonan bulaaf rabsaama turee qaman deemani Oroota qonaan bulaa dawaatan

17/08/2022

Yuunivarsitiin Haramaya Dameen Isportii Akadamiik sa'innsii ijjoolee Hawasa Naanno Alaa fi Kesaa ispoortii Gara Gaaratiin yeroo Boqqonna isaani lenjiisuu jalaqabe leenjiin kun ji'aa Tokkof akka turuu hiimame

05/08/2022

የመረጃ መዛባትን ሰዎች እንዲከላከሉ የሚያነቃቃ የንግግር መድረክ ተካሄደ፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ተሳትፎና ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ከሕግ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሚስተዋለውን ችግር ለመከላከልና ግጭቶችን ለመቀነስ የሚያስችል መድረክ ነው የተዘጋጀው፡፡

ሐምሌ 28/2014 ዓ.ም በአፍረን ቀሎ አዳራሽ በተዘጋጀው መድረክ ላይ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ተሳትፎና ኢንተርፕራይዝ ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይስሀቅ ዩሱፍ ባደረጉት ንግግር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከቀበሌ አንስቶ እስከ አገር አቀፍ ደረጃ በፖለቲካ ልዩነት፣ በብሔርና በሃይማኖት አክራሪነት እንዲሁም በድንበርና በሌሎች ሀብቶች ምክንያት ግጭቶች እንዲቀሰቀሱና እንዲባባሱ ማህበራዊ ሚዲያ ትልቅ ድርሻ እንደነበረው ጠቁመው በማህበራዊ ሚዲያና ተያያዥ ጉዳዮች ሳቢያ የሚስተዋለውን ችግር ለመከላከል እንዲቻል መድረኩ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።

ዶ/ር ይስሀቅ አክለውም እንደተናገሩት በአሁኑ ጊዜ በሰዎች መካከል የፖለቲካ ልዩነት፣ የብሔርና የሃይማኖት ልዩነቶች የግጭት መንስኤዎች ሊሆኑ የቻሉት የጥላቻ ንግግሮች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመስፋፋታቸውና ህብረተሰቡ እውነታውን ከማጣራት ይልቅ በቀላሉ እየተቀበለ በመሆኑ ግጭቶች እንዲከሰቱ ፣ የብዙ ወገኖቻችን ህይወት እንዲጠፋና ሰዎች ከቀዬአቸው እንዲፈናቀሉ ምክንያት ሆኗል።

ባለፉት ሶስት ወራት ይህንን ችግር ለማስቀረት እንዲቻል ከዩ ኤስ ኤይድ ጋር በመተባበር በኦሮሚያ ክልል በምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ዞኖች ፣ በሐረሪ ክልልና ድሬደዋ መስተዳደር የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን ለሀይማኖት አባቶች ፣ ለመንግስት ኮሙዩኒኬሽንና የሥራ ኃላፊዎች ፣ ተማሪዎችና ለዩኒቨርሲቲ ሠራተኞች መስጠቱን አስረድተዋል፡፡

በመድረኩ ላይ አቶ ብርሀኑ ራቦ 'የህይወት ሂደት መልሶ ግንባታ' በሚል ርዕስ እንዲሁም ወጣት መሐመድ አሊ ዩሱፍ (ቡርሀን አዲስ) 'በጥልቅ ማሰብና መረጃን መመዘን' በሚል ርዕስ አነቃቂ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የጥላቻ ንግግርን ማረቅ እንደሚያስፈልግና ሁሉንም መረጃ ሳያጣሩ እንዳለ መቀበል በህይወታችን ውስጥ ሀሳቦቻችንና በየቀኑ የምንወስዳቸው እርምጃዎቻችንን ስለሚያስቱ እንደ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ የተሳሳቱ መረጃዎችንና የጥላቻ ንግግሮችን ለመከላከል ለሚያስቻል የነቃ አእምሮ ሊኖረን ይገባል ብለዋል፡፡

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር መንግሥቱ ኡርጌ በበኩላቸው ማህበራዊ ሚዲያ ከእያንዳንዳችን ቤት ውስጥ ካሉት ህፃናት አንስቶ እሰከ በተማሩ ሰዎች ላይ ሁሉ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያደረሰ መሆኑን ጠቁመዋል።

በአሁኑ ጊዜ ሀሰተኛ መረጃዎች እንዲሁም የጥላቻ ንግግሮች በአገራችን ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም ላይ ከፍተኛ ችግር በመፍጠር ላይ እንደሚገኙ ፕሮፌሰር መንግስቱ ጠቅሰው የሀሰተኛ መረጃዎችንና የጥላቻ ንግግሮችን ለመቀነስ መሰል መድረኮች ማዘጋጀት ጠቀሜታው ከፍተኛ በመሆኑ ከመድረኩ ያገኘነውን እውቀት ወደተግባር በመቀየር ራሳችንን ለውጠን ለሌሎች መትረፍ ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡

የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
ዘጋቢ ፡ ሸምሸዲን መሀመድ
ፍቶግራፍ ፡ ፎአድ አህመድ አሊ
ሐምሌ28/ 2014 ዓ.ም

Address

Adama
093401

Telephone

+251920895648

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when YH fuad posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to YH fuad:

Share

Category