Sirara Marketing

Sirara Marketing Selling a Life lifestyle

ፖሊስ ዛሬ የሚዘጉ መንገዶችን እቁልኝ ብሏል  ⵑⵑ   | በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ ለሚደረገው የኢትዮጵያ ታምርት የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ለተሽከርካሪዎችና ለእግረኞች ዝግ የሚሆኑ መንገ...
27/04/2025

ፖሊስ ዛሬ የሚዘጉ መንገዶችን እቁልኝ ብሏል ⵑⵑ

| በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ ለሚደረገው የኢትዮጵያ ታምርት የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ለተሽከርካሪዎችና ለእግረኞች ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ፖሊስ እወቁልኝ ብሏል ፡፡

የውድድሩ መነሻ ቦታ መስቀል አደባባይ ሲሆን ለገሃር መብራት፣ ቡናና ሻይ ሜክሲኮ አደባባይ፣ አፍሪካ ህብረት ሳር ቤት (ፑሽኪን አደባባይ)፣ ቄራ አዲሱ መሿለኪያ ድልድይ፣ ጎተራ ማሳለጫ፣ አጎና ሲኒማ፣ ግሎባል ሆቴል፣ መስከረም ማዞሪያ፣ ጥላሁን አደባባይ፣ ሳንጆሴፍ መብራት አድርጎ መስቀል አደባባይ ያበቃል።

በዚህም መሠረት :-

* ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መስቀለኛ ላይ )

* ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)

* ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ)

* ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት

* ከብሔራዊ ቲያትር ወደ ለገሀር መብራት

* ከሠንጋ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ

* ከአረቄ ፋብሪካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ

* ከልደታ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ

* ከልደታ ፀበል ወደ አፍሪካ ህብረት መብራት

* ከካርል አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ

* ከቫቲካን ወደ ሳርቤት አደባባይ

* ከቄራ አልማዝዬ ሜዳ ወደ ቄራ መብራት

* ከጎፋ ገብርኤል አቅጣጫ ወደ ጎፋ መስቀለኛ በስር

* ከዮሴፍ ወደ ጎተራ ማሳለጫ

* ከመስቀል ፍላዎር ወደ አጎና መስቀለኛ

* ከጋዜቦ አደባባይ ወደ በቅሎ ቤት ድልድይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ይዘጋሉ።

በመስቀል አደባባይ ለሚከናወነው የኢፍጣር ፕሮግራም የተወሰኑ መንገዶች እንደሚዘጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ!   | ዛሬ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 5:00 ሠዓት ጀምሮ በመስቀል ...
16/03/2025

በመስቀል አደባባይ ለሚከናወነው የኢፍጣር ፕሮግራም የተወሰኑ መንገዶች እንደሚዘጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ!

| ዛሬ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 5:00 ሠዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ የሚከናወነውን የኢፍጣር ፕሮግራም ምክንያት በማድረግ፦

👉 ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ )

👉 ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ሲሆን ከባድ ተሽከርካሪ አጎና ላይ )

👉 ከለገሃር መብራት ወደ መሰቀል አደባባይ (ለገሃር መብራት)

👉 ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድየም (ቴሌ ማቋረጫ ላይ)

👉 ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ (ሀራምቤ መብራት ላይ )

👉 ከብሔራዊ ቤተ መንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ )

👉 ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መታጠፊያ ድረስ የሚዘጋ መሆኑን በመገንዘብ አሽከርካሪዎች አማራጭ እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ያሳስባል።

ዘገባ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ

 ሶሎዳ ፊልም ፕሮዳክሽን እና ልባም ፊልምስ ከዚህ በፊት በተመልካች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፉ "ልባም'' ፊልም እና "እርቅ ይሁን" የቴሌቪዥን ሾው በትብብር አቅርበዋል ። አሁን ደሞ ታህሳስ...
18/12/2024


ሶሎዳ ፊልም ፕሮዳክሽን እና ልባም ፊልምስ ከዚህ በፊት በተመልካች ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፉ "ልባም'' ፊልም እና "እርቅ ይሁን" የቴሌቪዥን ሾው በትብብር አቅርበዋል ።
አሁን ደሞ ታህሳስ 11 ጀምሮ የቀለም ጨዋታ ፊልምን ይዘው ቀርበዋል ።


ከ ታህሳስ 11 , 12 , 13 እና 18, 19 , 20 ጀምሮ በተመረጡ ሲኒማ ቤቶች መታየት ይጀምራል
የቀለም ጨዋታ
ፊልም
Getachew @
Temesgen Michael assefa
seyoum_haben
seyoum
(abu)

films
films

ሞዴል፡ ፋኦ ቬላሁኔታ፡ ጥሩ ይዞታትራንስሚሽን፡ ማንዋልከለር፡ አይጥማመኪናው ያለው፡ አ.አየተመረተበት ዓ.ም፡ 2012የሞተር መጠን፡ 1.5 ccዋጋ፡ 750,000 ብር + 2% ኮሚሽንመኪናውን ለ...
19/05/2023

ሞዴል፡ ፋኦ ቬላ
ሁኔታ፡ ጥሩ ይዞታ
ትራንስሚሽን፡ ማንዋል
ከለር፡ አይጥማ
መኪናው ያለው፡ አ.አ
የተመረተበት ዓ.ም፡ 2012
የሞተር መጠን፡ 1.5 cc
ዋጋ፡ 750,000 ብር + 2% ኮሚሽን
መኪናውን ለማየት በሚቀጥሉት ስልኮች ይደውሉ
0909336363 | 0984256296
ሲራራ ሽያጭና ማስተዋወቅ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በፓስተር ዮናታን አክሊሉ፣ በነቢይ ኢዩ ጩፋ እና የሚያገለግሉበት ቤተ ክርስቲያን ላይ ክስ መሠረተች======= #=======ረቡዕ ታሕሳስ 12 ቀን...
21/12/2022

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በፓስተር ዮናታን አክሊሉ፣ በነቢይ ኢዩ ጩፋ እና የሚያገለግሉበት ቤተ ክርስቲያን ላይ ክስ መሠረተች
======= #=======

ረቡዕ ታሕሳስ 12 ቀን 2015 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በፓስተር ዮናታን አክሊሉ፣ በአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተ ክርስቲያን፣ በክራይስት አርሚ ኢንተርናሽናል ቤተ ክርስቲያን እና በነቢይ ኢዩ ጩፋ ላይ ክስ መሠረተች።

በቤተክርስቲያንቷ ሕግ አገልግሎት መምሪያ በኩል ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ዳይሬክቶሬት የተላከው ክስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ያነጣጠረ የጥላቻ ንግግርና አደገኛ የሆነ የሃይማኖትን ክብር የሚነካ የአምልኮ ሥርዓትና እምነትን የሚያንቋሽሽ የዘለፋ እና ሐሰተኛ ንግግር በመፍጠር ለሁከትና ብጥብጥ መነሻ የሚሆን ድርጊት በፈጸሙ ግለሰቦችና ተባባሪ ተቋማት ላይ የወንጀል ምርመራ እንዲጣራ የሚጠይቅ ነው።

👉የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የክስ ዝርዝር ከሥር ተያይዟል።

በአስደናቂ ክስተቶች የታጀበው የኳታሩ ዓለም ዋንጫ በፍፃሜው የደቡብ አሜሪካዋን አርጀንቲና ከአውሮፓዋ ፈረንሳይ አፋጧል***********************ለ28 ቀናት ከተለያዩ የአለማችን አህ...
18/12/2022

በአስደናቂ ክስተቶች የታጀበው የኳታሩ ዓለም ዋንጫ በፍፃሜው የደቡብ አሜሪካዋን አርጀንቲና ከአውሮፓዋ ፈረንሳይ አፋጧል
***********************
ለ28 ቀናት ከተለያዩ የአለማችን አህጉራት የተወጣጡ 32 ብሔራዊ ቡድኖች በበረሃማዋ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገር ኳታር ሲፋለሙ ሰንብተው እንሆ ሁለት ቡድኖች ከፍፃሜው ደርሰዋል።
አርጀንቲና ከፈረንሳይ የአለምን እግርኳስ ዘውድ ለመድፋት በኳታር ከተገነቡት ዘመናዊ ስታዲየሞች አንዱ በሆነው በሉሳይል አይኮኒክ ስቴዲየም ምሽት 12 ሰዓት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
አርጀንቲና ገና በምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋ በሳውዲ አረቢያ አስደንጋጭ ሽንፈት ቢገጥማትም በቁርጥ ቀን ልጇ ሊዮኔል ሜሲ እየተመራች ከሽንፈቷ አገግማ ከፍፃሜው ደርሳለች።
ከዚህ በፊት በተደረጉት የ1978ቱ እና የ1986ቱ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ መሆን የቻለችው አርጀንቲና በምሽቱ ጨዋታ ለ36 አመታት የራቃትን ዋንጫ በድጋሚ ለማንሳት ትፋለማለች።
ቡድናቸው ለፍፃሜ የደረሰው የአርጀንቲናው ወጣት
አሰልጣኝ ሊዮኔል ስካሎኒ "ተጫዋቾቼ እዚህ ለመድረስ የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል በዚህም ሊኮሩ ይገባል" ብለዋል።በምሽቱ ጨዋታም አገራቸውን ወደራቃት ክብር ለመመለስ እንደሚጫወቱ ተናግረዋል።
በአንፃሩ ክዋክብትን ያሰባሰበው እና የ2018ቱን የአለም ዋንጫ ያነሳው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በምድብ ጨዋታ ማለፋቸውን ካረጋገጡ በኋላ በቱኒዚያ ከመሸነፋቸው ውጭ ሁሉንም ጨዋታዎች በበላይነት አጠናቀው ለፍፃሜው ደርሰዋል።
ከዚህ በፊት ሁለት ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማንሳት የቻለችው ፈሰንሳይም እንደ አርጂንቲና ለ3ተኛ ጊዜ ዋንጫውን ለማንሳት ትጫወታለች።
የ1998ቱን ዋንጫ ያነሳው ቡድን ተጫዋች በሆኑት ዲዲየር ዴሻምፕ የ2018ቱን የዓለም ዋንጫ ፈረንሳይን በአሰልጣኝነት እየመሩ ማሳካት ችለዋል ።ዘንድሮም ለፍፃሜው የደረሰው ቡድን አሰልጣኝ እኝሁ ዲዴየር ዴሻምፕ ናቸው።
አሰልጣኙ ከጨዋታው በፊት በሰጡት አስተያየት ቡድናቸው ውስጥ የተወሰኑ ተጫዋቾች በጉንፋን መሠል ቫይረስ እንደተጠቁ አንስተው ለምሽቱ ጨዋታ እንዲደርሱ የህክምና ቡድናችን የቻለውን እያደረገ ነው
ብለዋል።
ከ1962ቱ የብራዚል ብሔራዊ ቡድን በኋላ ዋንጫውን በተከታታይ ለማንሳት እንደሚጫወቱም ተናግረዋል።
በጨዋታው የፈረንሳዩ ክለብ ፒኤስጂ ተጫዋቾች የሆኑት አርጀንቲናዊው ሊዮኔል ሜሲና የፈረንሳዩ ኬሊያን ምባፔ ልዩነት ፈጣሪ ይሆናሉ ተብለው ከሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች በኩል ይጠበቃሉ።
አርጀንቲና እና ፈረንሳይ ከዚህ ቀደም 12 ጊዜ የተገናኙ ሲሆን አርጀንቲና 6 ጊዜ በማሸነፍ የበላይነቱን ትይዛለች፤ ፈረንሳይ በአንፃሩ 3 ጊዜ ድል ቀንቷታል። ቀሪዎቹ 3 ጨዋታዎች በአቻ ውጤት የተጠናቀቁ ናቸው።

የአርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ ( #ባባ) ሥርዓተ ቀብር በዛሬው እለት ቤተሰቦቹ ፣ አብሮ አደጎቹ ፣ የስራ ባልደረቦቹ ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድ...
12/12/2022

የአርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ ( #ባባ) ሥርዓተ ቀብር በዛሬው እለት ቤተሰቦቹ ፣ አብሮ አደጎቹ ፣ የስራ ባልደረቦቹ ፣ ወዳጅ ዘመዶቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።

Credit : ETHIOPIA PRESS AGENCY

Address

Adiss Ababa
Adama
1000

Telephone

+251909336363

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sirara Marketing posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sirara Marketing:

Shortcuts

Share