27/04/2025
ፖሊስ ዛሬ የሚዘጉ መንገዶችን እቁልኝ ብሏል ⵑⵑ
| በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ ለሚደረገው የኢትዮጵያ ታምርት የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ለተሽከርካሪዎችና ለእግረኞች ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ፖሊስ እወቁልኝ ብሏል ፡፡
የውድድሩ መነሻ ቦታ መስቀል አደባባይ ሲሆን ለገሃር መብራት፣ ቡናና ሻይ ሜክሲኮ አደባባይ፣ አፍሪካ ህብረት ሳር ቤት (ፑሽኪን አደባባይ)፣ ቄራ አዲሱ መሿለኪያ ድልድይ፣ ጎተራ ማሳለጫ፣ አጎና ሲኒማ፣ ግሎባል ሆቴል፣ መስከረም ማዞሪያ፣ ጥላሁን አደባባይ፣ ሳንጆሴፍ መብራት አድርጎ መስቀል አደባባይ ያበቃል።
በዚህም መሠረት :-
* ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መስቀለኛ ላይ )
* ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)
* ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ)
* ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት
* ከብሔራዊ ቲያትር ወደ ለገሀር መብራት
* ከሠንጋ ተራ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
* ከአረቄ ፋብሪካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
* ከልደታ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ
* ከልደታ ፀበል ወደ አፍሪካ ህብረት መብራት
* ከካርል አደባባይ ወደ ሳር ቤት አደባባይ
* ከቫቲካን ወደ ሳርቤት አደባባይ
* ከቄራ አልማዝዬ ሜዳ ወደ ቄራ መብራት
* ከጎፋ ገብርኤል አቅጣጫ ወደ ጎፋ መስቀለኛ በስር
* ከዮሴፍ ወደ ጎተራ ማሳለጫ
* ከመስቀል ፍላዎር ወደ አጎና መስቀለኛ
* ከጋዜቦ አደባባይ ወደ በቅሎ ቤት ድልድይ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ይዘጋሉ።