Tofik kedir

Tofik kedir peace &love

የትግራይ ህዝብ የህወሃት እስረኛ ሆኖ ሊቀጥል አይግባም ሲሉ ቢልለኔ ስዩም ተናገሩየሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴ ለሰሜኑ ግጭት ሰላማዊ እልባት ለመስጠት ያፀደቀው የሰላም ምክረ ሃሳብ መንግስት ለ...
19/08/2022

የትግራይ ህዝብ የህወሃት እስረኛ ሆኖ ሊቀጥል አይግባም ሲሉ ቢልለኔ ስዩም ተናገሩ

የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴ ለሰሜኑ ግጭት ሰላማዊ እልባት ለመስጠት ያፀደቀው የሰላም ምክረ ሃሳብ መንግስት ለሰላማዊ አማራጭ ያለውን ቁርጠኝነት ያረጋገጠ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታርያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገልጸዋል።ኃላፊዋ ለአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ስለ ሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ለተከሰተው ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ በመስጠቱ ዙሪያ፥ በመጪዎቹ ሳምንታት የተኩስ አቁም እንዲደረስ፣ የሰላም ውይይት እንዲሁም ሌሎች በእንጥልጥል የቀሩ ጉዳዮች ደግሞ በብሄራዊ ምክክሩ እንዲዳሰሱ ለማድረግ የሚያስችል የሰላም ረቂቅ ሰነድ ይፋ መደረጉን አንስተዋል፡፡

የሰላም ውይይት ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ የሚያስፈልገው አይደለም ያሉት ቢልለኔ፥ የትግራይ ህዝብ የህወሃት እስረኛ ሆኖ ሊቀጥል አይግባም ብለዋል፡፡ህወሃት በህገወጥ መንገድ የሰበሰበውን የውጭ ምንዛሪ፣ ለመጠባበቂያነት የተቀመጡ የነዳጅ፣ የምግብና የመሳሰሉ ግብአቶችን ለዚሁ እኩይ ተልዕኮው እንደሚጠቀም ጠቁመዋል።ቡድኑ ይህን ሁሉ እኩይ ተግባራት እየፈፀመ ባለበት ሁኔታ መንግስት ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ነገሮችን በሆደ ሲፊነት ሲመለከት መቆየቱን ተናግረዋል፡፡

መንግስትየሰላም ጥረቶችን ሲያደርግ እንደቆየና በህወሃት በኩል ለሰላም አማራጭ የተሰጠ ሥፍራ አለመኖሩን ገልጸዋል።ህወሃት የሀሰት ክሶችን በማንሳትና የተሳሳቱ ትርክቶችን በመንዛት ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ በተሳሳተ አቅጣጫ ለመምራት ሙከራ እያደረገ እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡ በትግራይ ክልል ዙሪያ ብዥታ ሊኖር እንደማይገባና በክልሉ መልሶ ግንባታና መሰረታዊ ድጋፎች ላይ መንግስት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡

03/08/2022
ባለፈው ዓመት የሚያበረታታ የወጪ ንግድ አፈጻጸም እና ቀጥተኛ የውጭ መዋዕለ ንዋይ ፍሰት ጭማሪ ታይቷል -ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ   አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 27 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፈው ዓ...
03/08/2022

ባለፈው ዓመት የሚያበረታታ የወጪ ንግድ አፈጻጸም እና ቀጥተኛ የውጭ መዋዕለ ንዋይ ፍሰት ጭማሪ ታይቷል -ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 27 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፈው ዓመት የሚያበረታታ የወጪ ንግድ አፈጻጸም እና ቀጥተኛ የውጭ መዋዕለ ንዋይ ፍሰት ጭማሪ መታየቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለፁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ ስብሰባውን ማካሄዱን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል።

በዚህ ወቅትም ባለፈው ዓመት የሚያበረታታ የወጪ ንግድ አፈጻጸም እና ቀጥተኛ የውጭ መዋዕለ ንዋይ ፍሰት መጨመር መታየቱን ጠቅሰዋል።

ባለፉት ሁለት ወራት የዋጋ ግሽበት መቀነስ፣ ከፍተኛ የአረንጓዴ አሻራ ክንውን፣ የበጎ ፈቃደኝነት ተግባራት፣ ወደ ሀገር ውስጥ የሚላክ የውጭ ምንዛሬ ጭማሪ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የሥራ ክንውኖች የተመዘገቡበት እንደሆነም ነው ያስታወቁት።

በዚህ ዓመትም የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ መቀጠል በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑንም አስገንዝበዋል።

አባይ እንደ ኑክሌየር ቦንብ አስፈሪ ሆኗል !እድለኛው ግድብ፣ ……………………………………………« የአልጀዚራ ጋዜጠኛ »ተፈጥሮ ተገዳ ሳይሆን አገሪቱ አስገድዳ እድለኛ አድርገዋለች። ወታደርም መሳሪያ...
01/08/2022

አባይ እንደ ኑክሌየር ቦንብ አስፈሪ ሆኗል !

እድለኛው ግድብ፣
……………………………………………
« የአልጀዚራ ጋዜጠኛ »

ተፈጥሮ ተገዳ ሳይሆን አገሪቱ አስገድዳ እድለኛ አድርገዋለች። ወታደርም መሳሪያም ዘበኛም አያስፈልገውም ። ማንም የምድራችን ሀይለኛ ነኝ የሚል መሳሪያ አይነካውም።

ምናልባት አንድ አውቶሚክ ሊዳፈረው ይችላል

ለሱ የተላከው ቦንቡ አንድ ግድብ ብቻ ነው የሚነካው። ጥቃት የተሰነዘረበት ግድብ ግን ለጥቃቱ የሚሰጠው መልስ ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎችንና የሁለት አገር ትልልቅ ከተሞችን ማለትም የሱዳንን ዋና ከተማ ካርቱምን ፣ የግብፅን ዋና ከተማ ካይሮን ያለምንም ከልካይ፣ አፍረሶ ወደ አፈር ቀይሮ ከውሀ ጋር ቀላቅሎ ነጭ ባህር ይጨምራል

ማንኛው የአለማችን መሳሪያ ነው ከኢትዮጵያ እስከ ነጭ ባህር ድረስ ከተሞችንና የመሰረተ ልማቶችን ህዝቦችን እየጠራረገ ነጭ ባህር የሚዶለው .? እስካሁን ድረስ ይህ መሳሪያ ያለው ኢትዮጵያ ውስጥ ጉባ ተራራ ሸለቆ ላይ የተጠመደ፣ አንድ አፍሪካዊ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብ፣ መሳሪያም ወታደርም ዘበኛም የማያስፈልግ እድለኛው የአባይ ግድብ ብቻ ነው። አዎ አንተ እድለኛ ነህ
በአለማችን ላይ ከህፃናት እስከ አዋቂዎች ስምህን የሚያውቁት ! ራስን በራስህ ያስከበርክ ‼

01/08/2022
29/07/2022

የአልሻባብ ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳ ኃላፊ ፏአድ መሐመድ ከሌፍን ጨምሮ ሶስት የቡድኑ አመራሮች ተደመሰሱ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 22 ፣ 2014 የአልሻባብ ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳ ኃላፊን ፏአድ መሐመድ ከሌፍ (ሼንጎሌ) ጨምሮ ሶስት የቡድኑ አመራሮች መደምሰሳቸውን የመከላከያ ኃይል ስምሪት ኃላፊና ጊዜያዊ የፀጥታ ኮማንድፖስት አስተባባሪ ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው ተናገሩ።

ሜጀር ጀኔራል ተስፋዬ ለኢዜአ እንደተናገሩት ባለፉት ቀናት ከኢፌዴሪ አየር ኃይል ጋር በመቀናጀት በተወሰደው እርምጃ የሽብር ቡድኑ ኢትዮጵያን ለማጥቃት ያዘጋጃቸውን የትጥቅና ስንቅ ዴፖዎች ማውደም ተችሏል፡፡

በተጨማሪም የአሸባሪ ቡድኑ አመራሮችና ታጣቂዎች በተወሰደው እርምጃ ተደምስሰዋል።

ከተደመሰሱት ውስጥ የአልሸባብ ከፍተኛ ኮማንደሮች ውስጥ:-

1. ፏአድ መሐመድ ከለፍ (ሼንጎሌ) የአልሸባብ ቅስቀሳና ፕሮፓጋንዳ ሃላፊ፣

2.አብዱላዚዝ አቡ ሙሳ የአልሸባብ ቃል አቀባይ፣

3.ኡቤዳ ኑር ኢሴ የአልሸባብ የቦኮል ዞንና የኢትዮጵያ ድንበሮች አዋሳኝ ሃላፊ መደምሰሳቸውን ሜጀር ጄኔራል ተስፋዬ ለኢዜአ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያዊነት አሸናፊነት ካልሆነ ሽንፈትን አጥብቃ የምትፀየፍ የኩሩዎች ሀገር
28/07/2022

ኢትዮጵያዊነት አሸናፊነት ካልሆነ ሽንፈትን አጥብቃ የምትፀየፍ የኩሩዎች ሀገር

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tofik kedir posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tofik kedir:

Share

Category