Memiher Mesfin Hailu

Memiher Mesfin Hailu ይህ የመምህር መስፍን ኃይሉ መንፈሳዊ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን እንዲሁም ወቅታዊ መልዕክቶችን የማስተላልፍበት የፌስ ቡክ ገፄ ነው።

ትህትና እውቀት ደግሞ የተወደደ ጸጋ ሁሉ የተስማማላቸው ቤተ ክርስቲያን ከልባቸው የሚወዷት የሚጥር ሰው ሲያዪ ከመደገፍ ወደ ኋላ የማይሉ ሁሌ መማር የሚወዱ ደግሞም ተወዳጅ አባት መልካም እረኛ...
17/06/2026

ትህትና እውቀት ደግሞ የተወደደ ጸጋ ሁሉ የተስማማላቸው ቤተ ክርስቲያን ከልባቸው የሚወዷት የሚጥር ሰው ሲያዪ ከመደገፍ ወደ ኋላ የማይሉ ሁሌ መማር የሚወዱ ደግሞም ተወዳጅ አባት መልካም እረኛ በእውነት ስለ እርሶ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁኝ።
እንኳን ደስ አሎት አባቴ መካሪዬ የለጠ ስራ እንዲሰሩ ለበለጠው ማዕረግ ከፍ ብለው ባይ ምኞቴ ነው።

🔥 🍀ወጣትነት ለቤተ ክርስቲያን! 🍀🔥🔥🕜5ኛ ዓመት የምስታ በዓል መንፈሳዊ  ጉባኤ🕜🔥      🙏እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን🙏🍀 "በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ"🍀                 ...
15/06/2026

🔥 🍀ወጣትነት ለቤተ ክርስቲያን! 🍀🔥

🔥🕜5ኛ ዓመት የምስታ በዓል መንፈሳዊ ጉባኤ🕜🔥
🙏እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን🙏

🍀 "በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ"🍀
መክ 12፥1

ታላቁ የልማት የወንጌል አባት በሆኑት ብፁዕ አባታችን አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ታላቁ የልማትና የወንጌል አባት ወጣትነት ለቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ጉባኤ በብፁነታቸው አዘጋጅነት ከሰኔ 19 እስከ 21/2018 ዓ.ም በሰበታ መካነ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ታላቅ ድምቀት ይከበራል።

🙏🔥ወጣቶች ሆይ🔥🙏
ወጣቶች ሆይ! እግዚአብሔር ይጠራቹሃል!!!
➦ዓለም ወጣትነታችንን ለራሷ ልትወስድ ትፈልጋለች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ሕይወታችንን ለማዳን ይጠራናል።

➦ዛሬ ቤተ ክርስቲያናችን የምትፈልገው ተመላላሽ ሳይሆን ወደ እግዚአብሔር የሚመለስ፣ ተመልካች ሳይሆን አገልጋይ፣ ተከታይ ሳይሆን መሪ፣ ሰሚ ሳይሆን የወንጌል ምስክር የሚሆን ወጣት ነው። በመሆኑም በወንጌል እንዲህ ተብሏል፦
🍀" በቃልና በኑሮ በፍቅርም በእምነትም በንጽሕናም ለሚያምኑቱ ምሳሌ ሁን እንጂ፥ ማንም ታናሽነትህን አይናቀው። 1ኛ ጢሞ 4፥11-12 ስለዚህም፦
🔥ወጣቶች ሆይ ኑ👐🔥
✔በጸሎት እንበርታ
✔በቃሉ እንታነጽ
✔ቃሉን በማድመጥ ንስሀ እንግባ
✔በፍቅር እንተሳሰር
✔በአገልግሎት እንትጋ
📣 ሁላችሁም በዚህ ዓመታዊ ልዩ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ እንድትሳተፉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር ጥሪዬን አስተላልፋለሁኝ።
⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪
ይህ መልዕክት ለሁሉ እንዲዳረስ ሼር አድርጉ
⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪⛪
ሰኔ 08/2018 ዓ.ም
መ/ር መስፍን ኃይሉ

⛪በጥታዊውና በታሪካዊው ቤተ መቅደስ⛪     በሸገር ሀገረ ስብከት በሰበታ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የሜታፈለገ ሕይወት አቡነ ገብረ  መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት...
14/06/2026

⛪በጥታዊውና በታሪካዊው ቤተ መቅደስ⛪
በሸገር ሀገረ ስብከት በሰበታ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የሜታፈለገ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት ዕለት በቅዳሴው በአውደ ምህረቱም በወንጌልና በዝማሬ ስንባረክን አረፈድን በቃሉ ያሳረፈን በዝማሬው ያጽናናን እግዚአብሔር ይመስገን።
በደብረ ለስብከተ ወንጌል ትኩረት በመስጠት ከደብሩ አስተዳዳሪ ጀምሮ የአስተዳደር ሠራተኞቹ ፣የደብሩ ሰበካ ጉባኤ፣ ማህበረ ካህናቱ ፣ በቦታ ላይ ብዙ ልማት ላይ ትልቅ ተሳትፎ የሚያደርጉ የጻድቁ ልጆች ዲያቆናት ለጉባኤው ያላቸው ትጋት እጅግ ይማርካል። ምዕመና በመረጋጋት ወንጌል ሲማሩ እንዴት እንደሚያምሩ እግዚአሔር በሀይማኖት ያጽናችሁ።
ይህን ጥታዊና ታሪካዊ ቤተ መቅደስ በደብሩ የሚሰሩትን ልማትን ለመደገፍ ከታች በማስቀምጥላችሁ አካውንት ገቢ በማድረግ የደብሩን ልማት እንድትደግፉ መንፈሳዊ መልዕክቴን አስተላልፋለሁኝ።
➦⛪1000016004042. ሜታ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን
የጻድቁ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን መልካም ዕለተ ሰንበት ይሁንልን።
ሰኔ 07/2018 ዓ.ም
መ/ር መስፍን ኃይሉ

02/06/2026
31/05/2026

እንኳን አደረሳችሁ ይህን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ

ዲያቆን ዘማሪ ፍቅረ ሥላሴ ሙሉ እጅግ ልዩ ጸጋ ያለክ ወንድሜ በርታል መዝሙር እንዴት እንደሚገዛ ጸጋህን ያብዛ   ተወዳጆች በቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን ይህን መዝሙር እንድታደምጡት እጋብዛቹ...
31/05/2026

ዲያቆን ዘማሪ ፍቅረ ሥላሴ ሙሉ እጅግ ልዩ ጸጋ ያለክ ወንድሜ በርታል መዝሙር እንዴት እንደሚገዛ ጸጋህን ያብዛ
ተወዳጆች በቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን ይህን መዝሙር እንድታደምጡት እጋብዛቹሃለሁኝ ስለምታደምጡትም ከልብ አመሰግናለቱኝ።
መንፈስ ቅዱስ

ፈኑ ጸጋ መንፈስ ቅዱስፈኑ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ላዕሌነእንድንበረታ ጸንተን በአንድነትእንድንበረታ ሆነን በእምነት"ያለ መንፈስ ቅዱስ የጥብዓት ስጦታበቄሳር ፊት ማለት ኢየሱስን 'ጌታ'አ.....

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ሊቀ ጳጳስበዓለ ጰራቅሊጦስን አስመልክተው ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህ...
31/05/2026

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ሊቀ ጳጳስ
በዓለ ጰራቅሊጦስን አስመልክተው ያስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት


ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አሰኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ በዓለ ጰራቅሊጦስ እና የሰንበት ት/ቤቶች ቀን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልእከት አስተላለፉ።

እውነትም ሰበታ መካነ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ይለያል “አቤቱ፥ ለስምህ ክብር ስጥ እንጂ፥ ለእኛ አይደለም”       መዝ 114፥1 ተብሎ እንደተጻፈ፤➦🍀በዚህ ቆይታዬ የተደረገው...
28/05/2026

እውነትም ሰበታ መካነ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ይለያል

“አቤቱ፥ ለስምህ ክብር ስጥ እንጂ፥ ለእኛ አይደለም” መዝ 114፥1 ተብሎ እንደተጻፈ፤
➦🍀በዚህ ቆይታዬ የተደረገው ሁሉ በጸጋው እንጂ በእኔ ኃይል አይደለም የሰራ ያከናወነ የዘለዓለም አምላክ እግዚአብሔር ይመስገን።

➦🍀4 ዓመት ቆይታዬ በዚህ ወንጌል ወዳድ ደብር በስብከተ ወንጌል ማገልገል ስብከተ ወንጌል አገልጋይ ኃላፊ መሆን ብቻ አልነበረም፤ የሕይወት ትምህርት ነበር። በዚህ ደብር የተማርኩት ካስተማርኩት ይበልጣል።

➦🍀ከአባቶቼ ትሕትናን ተምሬአለሁ፣
ከምዕመናን ፍቅርን ተምሬአለሁ፣
ከአገልጋዮች ትጋትን ተምሬአለሁ። በፊል 1፥3
“ባሰብኋችሁ ጊዜ ሁሉ አምላኬን አመሰግናለሁ” ይላል። እኔም ዛሬ ስለ እናንተ ሳስብ ልቤ በምስጋና ይሞላል።
ክቡራን አባቶች በጸሎታችሁ ደግፋችሁኛል፣
በምክራችሁ አቅንታችሁኛል፣ በፍቅራችሁ አበርትታችሁኛል ከልብ አመሰግናለሁኝ።
ይህን ውለታ የምረሳው አይደለም የተወደዳችሁ ምዕመናን፤ እናንተ ለእኔ ተሰብቦ ወንጌል የሚማር ብቻ አልነበራችሁም፤ የልቤ ቤተሰብ ሆናችኋል። በደስታችሁ ደስ ብሎኛል፣ በሐዘናችሁ አልቅሻለሁ፣ በጸሎታችሁ ተጠብቄአለሁ። በሐዋ 20፥31
“ሌሊትና ቀን በእንባ እየመከርሁ አላቋረጥሁም” እንዳለ፤ እኔም በዚህ ወንጌል ወዳድ ሀይማኖት ወዳጅ ደብር በእንባ፣ በጸሎት፣ በፍቅር ያለፉ ብዙ ቀናት አሉኝ።
ዛሬ ከዚህ ቦታ ብለይም፣ ከፍቅራችሁ አልለይም። ምክንያቱም የክርስቶስ ፍቅር በቦታ አይወሰንም።
በአገልግሎቴ ወቅት በቃል ወይም በተግባር ያሳዘንኳችሁ ነገር ካለ በክርስቶስ ፍቅር ይቅር በሉኝ።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
ለመካነ ሰላም ሰበታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ያለኝ ልዩ መልዕክት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ 2ኛ ቆሮንቶስ 13፥11 “በአንድነት ኑሩ፤ የፍቅርና የሰላም አምላክም ከእናንተ ጋር ይሆናል” እንዲል፤ እባካችሁ በፍቅር ኑሩ፣ ቤተ ክርስቲያንን አገልግሉ፣ ጸሎትን አትተዉ፣ እምነታችሁን ጠብቁ መልዕክቴ ነው።

በመቀጠልም ይህ ብዙ አገልጋዮችን ያፈራ ደብር የወንጌል ብርሃን በዚህ ስፍራ አይጥፋ፤
እግዚአብሔር አባቶቻችንን ይጠብቅ፣ ምዕመናኑን ይባርክ፣ ወጣቶችን በፍርሃቱ ያጽና።
🙏🍀በመጨረሻም🍀🙏
ሰው ከደብር ሊሄድ ይችላል፤ ነገር ግን ከልብ የተጻፈ ፍቅር አይጠፋም።
እኔ ከዚህ ስፍራ ብለይም ልቤ ግን ሁሌ ከእናንተ ጋር ይኖራል። የደብሩ ሰበካ ጉባኤና የአስተዳደር ሰራተኞች በአገለገልኩት ሕዝብ ፊት ስላከበራችሁኝ እግዚአብሔር ያክብርልኝ።
ሐዋርያ ሂያጅ ነውና እኛም የሐዋርያት በረከት አድሮብን ይህ የአገልግሎት ዘመን ከተሰጠን እንደነሱ እየዞርን ከከተማ እስከ ገጠር ማገልገል ግዴታ አለብንና ስለ ወደፊት አገልግሎቴ በጸሎታችሁ እንድታስቡኝ እላለሁኝ።አሜን
✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥
ሁላችሁንም እግዚአብሔር ያክብርልኝ ክፉ አይንካችሁ
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
መ/ር መስፍን ኃይሉ
ግንቦት 20/2018 ዓ.ም

25/05/2026

በዓለምገና ደብረ ሲና ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ወርሃዊ የቅድስት ኪዳነ ምህረት ጉባኤያችን በማለዳው አገልግሎት
ዘማሪ ሚክያስ አረጋዊ

Address

Addis Ababa
1000

Telephone

+251913791443

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Memiher Mesfin Hailu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category