Memiher Mesfin Hailu

Memiher Mesfin Hailu ይህ የመምህር መስፍን ኃይሉ መንፈሳዊ ትምህርቶችንና ዝማሬዎችን እንዲሁም ወቅታዊ መልዕክቶችን የማስተላልፍበት የፌስ ቡክ ገፄ ነው።

🏫🌴ዮም ንወድሳ ለማርያም🌴🏫  በዓለም ገና ደብረ ሲና ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን የጾመ ማርያም የዕለተ ሰንበት አገልግሎት ሌሊት በሰዓታቱ በስብሐተ ነጉ በመዝሙሩ በቅዳሴው እንዲሁም...
09/08/2026

🏫🌴ዮም ንወድሳ ለማርያም🌴🏫
በዓለም ገና ደብረ ሲና ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን የጾመ ማርያም የዕለተ ሰንበት አገልግሎት ሌሊት በሰዓታቱ በስብሐተ ነጉ በመዝሙሩ በቅዳሴው እንዲሁም በአውደምህረቱ በውዳሴ ማርያም እና ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ በመቀጠልም በወንጌሉ እና በዝማሬው ተባርከተን በደብራችን አስተዳዳሪ ቃለ ምዕዳን ቡራኬ ተሰጥቶ የማለዳው ጉባኤያችን ተጠናቋል።
🙏 ጾማችን እና ጸሎታችን እግዚአብሔር ይቀበለን።
ነሐሴ 03/2018 ዓ.ም
መ/ር መስፍን ኃይሉ

09/08/2026
🏫"እግዚአብሔር ቃል ነፍስን ሥጋን ከአንቺ ነስቶ ሰው የሆነ ሙሽራ ከጫጉላው እንዲወጣ ከአንቺ የተገኘ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ"🏫            ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅበሸገር ሀገረ ስብከት...
07/08/2026

🏫"እግዚአብሔር ቃል ነፍስን ሥጋን ከአንቺ ነስቶ ሰው የሆነ ሙሽራ ከጫጉላው እንዲወጣ ከአንቺ የተገኘ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ"🏫
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

በሸገር ሀገረ ስብከት በፉሪ ክፍለ ከተማ የፉሪ ደብረ ከዋክብት ቅድስት ልደታ ማርያም እና ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ወርሃዊ የቅድሰት ልደታ ለማርያም የጾመ ፍልሰታ የመጀመሪያ ቀን የማለዳ ጉባኤ በሰዓታቱ ስንባረክ አድረን በጠዋቱ ደግሞ በዝማሬው እግዚአብሔርን ስናመሰግን በቃለ ወንጌሉ ስንጽናና አረፈድን ይህን የተወደደ ጊዜ የሰጠን እግዚአብሔር ይመስገን። የወላዲተ አምላክ የቅድስት ድንግል ማርያም ጣዕሟ ፍቅሯ ይደርብን። ጾሙን ምህረት የምናገኝበት ያድርግልን
ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም
መ/ር መስፍን ኃይሉ

እንኳን ለጾመ ማርያም(ጾመ ፍልሰታ)አደረሳችሁ 🙏አምላካችን እግዚአብሔር የምሕረት ፊቱን ይመልስልን🙏 "ፅንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና  እመቤታችን ፀጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን! ...
07/08/2026

እንኳን ለጾመ ማርያም(ጾመ ፍልሰታ)አደረሳችሁ

🙏አምላካችን እግዚአብሔር የምሕረት ፊቱን ይመልስልን🙏

"ፅንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን
ፀጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኝልን! አእምሮውን ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን ! "

በዚህ የጾም ወቅት እንደ ቀደሙት ደጋግ ቅዱሳን መልስ የምናገኝበት ጾም ያድርግልን!!!
ነሐሴ 01/2018 ዓም
መ/ር መስፍን ኃይሉ

ትሁት ቅን አገልግሎት አክባሪ ወንድም ወዳጅ ባለ ብዙ ጸጋ በሁሉ ተወዳጅ ወንድሜ ዲያቆን ዘርአዳዊት እንዳልካቸው በእውነት ለዚህ በመብቃትህ እጅግ ደስ ብሎኛል እንኳን ደስ ያለህ።     🌴አይ...
06/08/2026

ትሁት ቅን አገልግሎት አክባሪ ወንድም ወዳጅ ባለ ብዙ ጸጋ በሁሉ ተወዳጅ ወንድሜ ዲያቆን ዘርአዳዊት እንዳልካቸው በእውነት ለዚህ በመብቃትህ እጅግ ደስ ብሎኛል እንኳን ደስ ያለህ።
🌴አይቀርም ለሁሉ እንዲዳረስ ሼር አድርጉት🌴

🏫 በዳሊቲ ማረሚያ ቤት የነበረን አገልግሎት🏫  "ዑራኤል የተባለ መልአከ ሊረዳኝ መጣ"                      ዕዝ. ሱቱ 2፥1  በሸገር ሀገረ ስብከት በሰበታና ገላን ጉዳ ፉሪ ክፍ...
30/07/2026

🏫 በዳሊቲ ማረሚያ ቤት የነበረን አገልግሎት🏫

"ዑራኤል የተባለ መልአከ ሊረዳኝ መጣ"
ዕዝ. ሱቱ 2፥1
በሸገር ሀገረ ስብከት በሰበታና ገላን ጉዳ ፉሪ ክፍላተ ከተማ የዳለቲ ማረሚያ ቤት የቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሸገር ከተማ ዳለቲ ያለው ማረሚያ ቤት የቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በመታነፅ ላይ ይገኛል።
ብፁዕ አባታችን ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ስራ አስኪያጅ የሸገር ከተማና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የምስካየ ህዙና መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ የቦርድ ሰብሳቢ ወንጌላዊ የልማት አርበኛ መሰረተ ድንጋይ ከተቀመጠ በኋላ በሀገረ ስብከቱ እና በክፍለ ከተማ ልዩ ክትትል በሕንፃ አሰሪ ኮሚቴው ትጋት ወደ መጠናቀቁ ደርሶአል።
እኔም ከሌሎች አገልጋዮች ጋር በጋራ በመሆን በማረሚያ ቤቱ በመገኘት ቤተ ክርስቲያኒቷ የተሰየመችው በነጎድጓድ እና በመባርቅት ላይ የተሾመው መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ሐምሌ 22 ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበት ቀን በመሆኑ በስፍራው ተገኝተን ጸሎተ ኪዳን የወንጌልና የዝማሬ እንዲሁም በበገና በስነ ግጥም ከታራሚዎች ጋር እግዚአብሔርን ስናመሰግን ዋል።
እጅግ የበረከት ጊዜ ነበር ተስፋ የቆረጡ የተሰበሩ ብዙ ታራሚዎች በእንባ በተሞላ መንፈስ ሆነው ወደ ፈጣሪያቸው ሲማጸኑ ማየት ደግሞም በአገልግሎቱ ሲጽናኑ ስንመለከት በእውነት ስለዚህችም ቀን እግዚአብሔር ይመስገን።
ቤተ መቅደሱን ባለመጠናቀቁ ምክንያት ንስሃ የገቡ ሰዎች ሥጋና ደሙን እንዲሁም እዛው የተወለዱ ህፃናትና በዛ በማረሚያ ቤት ወደ ቅድስት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተመለሱትን ለማጥመቅ ህንፃው አልቆ ታቦተ ሕጉ ባለመግባቱ ክርስትና አልተነሱም በመሆኑም ህንፃው ሊጠናቀቅ ሚቀሩት ጥቂት ነገሮች ስለሆኑ በዚህ የበረከት ስራ ላይ እጃችሁን እንድትዘረጉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር እጠይቃቹሃለሁኝ።

ሕንፃ እንዲጠናቀቅ የሚያስፈልጉ

1ኛ መስታወት ለ 33 መስኮት እና 8 በሮች
2ኛ ኤለክትሪክ ገመድ 18 ጥቅል
3ኛ ኮርነስ 200 ካሬ ሜትር
4ኛ ምንጣፍ እና መብራት

🏫ዋጋ ዝርዝር🏫
➥የአንድ ካሬ መስታወት ዋጋ 2800 ነው
ሀ፦በአማካኝ የአንድ መስኮት ስፋት 2.5 × 2800= 7000 ሲሆን
በጥቅሉ ለመስኮት 2.5×2800×33= *231,000*
ለ፦ በአማካኝ የአንድ በር ስፋት 5.5×2800= 15400 ሲሆን
በጥቅሉ 5.5×2800×8= *123200*
በጥቅሉ ለመስታወት 354,200 ብር ይፈጃል
2ኛ የኤለክትሪክ ገመድ የአንዱ ዋጋ 12,000 ብር ስሆን
በጥቅል 12000×18= *216,000*
3ኛ ኮርነስ 200 ካሬ የአንዱ ካሬ ዋጋ 1500 ሲሆን
በጥቅሉ 200×1500= *300,000*
Total 231,000+123200+216,000+300,000= *870,200*
4ኛ ምንጣፍና መብራቱ እንደሚገዙት ሰዎች ይወሰና በመሆኑም ይህ ህንፃ እንዲጠናቀቅ የበኩላችን እንድንወጣ በፍቅር እጠይቃለሁኝ።

🙏የደብሩ አካውን🙏
1000611436983 ሸገር ማረሚያ ቤት ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን
ሐምሌ 23/2018 ዓ.ም
መ/ር መስፍን ኃይሉ

Address

Addis Ababa
1000

Telephone

+251913791443

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Memiher Mesfin Hailu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category