30/07/2026
🏫 በዳሊቲ ማረሚያ ቤት የነበረን አገልግሎት🏫
"ዑራኤል የተባለ መልአከ ሊረዳኝ መጣ"
ዕዝ. ሱቱ 2፥1
በሸገር ሀገረ ስብከት በሰበታና ገላን ጉዳ ፉሪ ክፍላተ ከተማ የዳለቲ ማረሚያ ቤት የቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሸገር ከተማ ዳለቲ ያለው ማረሚያ ቤት የቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በመታነፅ ላይ ይገኛል።
ብፁዕ አባታችን ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ስራ አስኪያጅ የሸገር ከተማና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የምስካየ ህዙና መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ የቦርድ ሰብሳቢ ወንጌላዊ የልማት አርበኛ መሰረተ ድንጋይ ከተቀመጠ በኋላ በሀገረ ስብከቱ እና በክፍለ ከተማ ልዩ ክትትል በሕንፃ አሰሪ ኮሚቴው ትጋት ወደ መጠናቀቁ ደርሶአል።
እኔም ከሌሎች አገልጋዮች ጋር በጋራ በመሆን በማረሚያ ቤቱ በመገኘት ቤተ ክርስቲያኒቷ የተሰየመችው በነጎድጓድ እና በመባርቅት ላይ የተሾመው መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ሐምሌ 22 ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበት ቀን በመሆኑ በስፍራው ተገኝተን ጸሎተ ኪዳን የወንጌልና የዝማሬ እንዲሁም በበገና በስነ ግጥም ከታራሚዎች ጋር እግዚአብሔርን ስናመሰግን ዋል።
እጅግ የበረከት ጊዜ ነበር ተስፋ የቆረጡ የተሰበሩ ብዙ ታራሚዎች በእንባ በተሞላ መንፈስ ሆነው ወደ ፈጣሪያቸው ሲማጸኑ ማየት ደግሞም በአገልግሎቱ ሲጽናኑ ስንመለከት በእውነት ስለዚህችም ቀን እግዚአብሔር ይመስገን።
ቤተ መቅደሱን ባለመጠናቀቁ ምክንያት ንስሃ የገቡ ሰዎች ሥጋና ደሙን እንዲሁም እዛው የተወለዱ ህፃናትና በዛ በማረሚያ ቤት ወደ ቅድስት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተመለሱትን ለማጥመቅ ህንፃው አልቆ ታቦተ ሕጉ ባለመግባቱ ክርስትና አልተነሱም በመሆኑም ህንፃው ሊጠናቀቅ ሚቀሩት ጥቂት ነገሮች ስለሆኑ በዚህ የበረከት ስራ ላይ እጃችሁን እንድትዘረጉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር እጠይቃቹሃለሁኝ።
ሕንፃ እንዲጠናቀቅ የሚያስፈልጉ
1ኛ መስታወት ለ 33 መስኮት እና 8 በሮች
2ኛ ኤለክትሪክ ገመድ 18 ጥቅል
3ኛ ኮርነስ 200 ካሬ ሜትር
4ኛ ምንጣፍ እና መብራት
🏫ዋጋ ዝርዝር🏫
➥የአንድ ካሬ መስታወት ዋጋ 2800 ነው
ሀ፦በአማካኝ የአንድ መስኮት ስፋት 2.5 × 2800= 7000 ሲሆን
በጥቅሉ ለመስኮት 2.5×2800×33= *231,000*
ለ፦ በአማካኝ የአንድ በር ስፋት 5.5×2800= 15400 ሲሆን
በጥቅሉ 5.5×2800×8= *123200*
በጥቅሉ ለመስታወት 354,200 ብር ይፈጃል
2ኛ የኤለክትሪክ ገመድ የአንዱ ዋጋ 12,000 ብር ስሆን
በጥቅል 12000×18= *216,000*
3ኛ ኮርነስ 200 ካሬ የአንዱ ካሬ ዋጋ 1500 ሲሆን
በጥቅሉ 200×1500= *300,000*
Total 231,000+123200+216,000+300,000= *870,200*
4ኛ ምንጣፍና መብራቱ እንደሚገዙት ሰዎች ይወሰና በመሆኑም ይህ ህንፃ እንዲጠናቀቅ የበኩላችን እንድንወጣ በፍቅር እጠይቃለሁኝ።
🙏የደብሩ አካውን🙏
1000611436983 ሸገር ማረሚያ ቤት ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን
ሐምሌ 23/2018 ዓ.ም
መ/ር መስፍን ኃይሉ