27/06/2023
ከአማራ ህዝባዊ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ‼️
የአማራ ህዝባዊ ኮሚቴ "የተደረገብንን አንረሳም!" በሚል መሪ ቃል ከዛሬ ከሰኞ ሰኔ 19/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት(3) ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የትምህርትና የስራ ማቆም አድማ በመላው አማራ ክልል መጥራቱ ይታወቃል ።
በዚህም የትምህርትና የስራ ማቆም አድማ (ጥሞና) በኦሮሙማ ፋሽስት አገዛዝ በግፍ ለተረሸኑ ሙስሊም እህት ወንድሞቻችን እና የኦርቶዶክስ መነኮሳት ፣መናንያን ፣ቀሳውስት እና አማኞች በህሊና ፀሎት ታስበው እንዲውሉ እና 12 የሚደረሱ አንኳር ጉዳዮችን ዓላማ ያደረገ መሆኑን በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያ መግለጻችን ይታወሳል፡፡
በዚህም በጎጃም (ማንኩሳ ፣አዲስ ቅዳም ፣ጅጋ ወዘተ ) ፣ጎንደር ከተማ እና አካባቢው( ገደብዬ ፣ሻውራ እና ሌሎችም ) በወሎ እና ሸዋ(ምንጃር ፥አረርቲ እና አካባቢው) በተወሰኑ ቦታዎች የአማራ ህዝባዊ ኮሚቴ የጠራው አድማ በከፍተኛ አፈና ወከባ ውስጥም ማድረግ ተችሏል ።በዚህ ምክንያት በደብረ ታቦር ከተማና አካባቢው ከተጠራው አድማ ጋር ተያይዞ በርካታ ወጣቶች ታስረዋል ።ከፍተኛ ወከባ እና እንግልት እንደ ደረሰባቸው ማረጋገጥ ችለናል ።
ነገር ግን አንዳንድ የአገዛዙ ተላላኪ ባንዳዎች፣የአማራን ትግል እኛ ካለመራነው ፣እኛ ካላወቅነው ፣እኛ ካላቦካነው አይጋገርም ባዮች እንደሚገልጹት ሳይሆን አድማው የተጠራው ትግሉን ህዝባዊ ለማድረግ ፣የትጥቅ ትግሉን ለመደገፍ እና የህዝባዊ እምቢተኝነት አንዱ ማሳያ ነው፡፡
የመጣውን ወራሪ የኦሮሙማ ሰራዊት በህዝባችን የህልውና አደጋ የደቀነ በመሆኑ ትግላችንም ህዝባዊ አድርገን ለማስወጣት የሚደረግ በአራቱም ማዕዘን እየተዋደቀ ለሚገኘው የአማራ ፋኖ ፤የአማራ ህዝባዊ ሀይል ደጀን ለመሆን በአማራ ህዝባዊ ኮሜቴ አስተባባሪነት የተጠራ አድማ ነው ።
ትግል ዘርፈ ብዙ ነው ።ሁሉም ማድረግ የሚችለውን የትግል አበርክቶ እንዲያደርግ መንገዶች መከፈት አለባቸው ። ወጣት ፣አዛውንት ፣ሴት ፣ወንድ ፤ነጋዴ ፣መምህራን ፣የመንግስት ሰራተኛ ከሊቅ እስከ ደቂቅ መሳተፍ እንዲችል መስራት ይገባል ።የገጠመን ፈተና እንደ ህዝብ ነው ፤ማሸነፍ የሚቻለው ትግላችንን ህዝባዊ በማድረግ ብቻ ነው ።
የአማራ ህዝባዊ ኮሚቴ እሰራ ያለው እንደ ክልል እንደ ህዝብ አንድ ሆነን መንቀሳቀስ እንድንችል ፣አንድ አይነት ሀሳብ ፣ ወጥ የሆነ እና በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት በአንድነት እንደ ህዝብ የምንነሳበትን የትግል ሥልት እንዲኖረን እየሰራን ነው ።ይህም ለቀጣዩ ምዕራፍ እንድንዘጋጅ ሊያደርግ የሚችል አሰራር ለመዘርጋት የተናበበ ፣የተቀናጀ እና በአንድነተ እንደ ህዝብ መነሳት እንድንችል የታሰበ ጭምር መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
ይሁን እንጅ ለአማራ ህዝብ እውነተኛ ተቆርቋሪ ነኝ በማለት ነገር ግን ለወደፊቱ ለወሳኙ ምዕራፍ የትግል እንቅስቃሴ ትልቅ እንቅፋት ማን ሊሆን እንደሚችል በትክክል መሬት ላይ ባገኘነው ሀቅ ተረድተናል ። ከብልጽግና ጥሬ የሚሰፈርላቸው የሰፈር ወጠጤዎች፣መንደርተኞች ፣የድራፍት ቤት ጀብደኞችን ያየንበት እንዲሁም የአማራን ህዝብ ክደው የብልጽግና እውነተኛ ካድሬዎችን የሆኑ በተለያዩ ቦታዎች ፣ በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲ አመራሮችን ጭምር በትክክል የለየነበት የትግል አቅጣጫ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡
የአማራ ህዝባዊ ኮሚቴ የሚሰራው መላው የአማራ ህዝብ ነጻነቱንና ህልውናውን እንዲያረጋግጥ ነው ።
የአማራ ህዝባዊ ኮሚቴ በጠራው አድማ ምክንያት ወገኖቻችን በኃይል ሱቅ እንዲከፍቱ መደረጉ፣ የቆመ መኪና፣ባጃጅ ታርጋ እንዲፈታ በተላላኪ ባንዳዎች መደረጉ እንግልቶች እየደረሰባቸው መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በተጨማሪም ህዝቡ ያቀረበውን ጥያቄ ግምት ውስጥ በማስገባት ፣የእስልምና እምነት ተከታዮች በመጪው እረቡ የሚያከብሩትን በዓል ምክንያት በማድርግ እና የአማራ ህዝብ ለወሳኙ ህዝባዊ የትግል ምዕራፍ ያሳየውን ቁርጠኝነት እና ዝግጅት በትክክል ያገናዘበ ሁኔታ በመኖሩ ከሰኔ 20/2015 ዓም ጀምሮ ሁሉም ወደ ሥራ ገበታው እንዲመለስ ጥሪ እያቀረብን ለወሳኙን እና ለመጨረሻውን ምዕራፍ የአማራ ህዝባዊ ትግል አስፈላጊ ዝግጅቶች እንዳለቁ ይፋ የምናደርግ መሆኑን እያሳወቅን ለወሳኙ ምዕራፍ ከዚህ የተሻለ ዝግጅት መላው ህዝባችን እንዲያደርግ እያሳሰብን ወደ ፊት ከህዝቡ የሚጠበቁ ዝርዝር ጉዳዮችን የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
በመጨረሻም በሁሉም ቦታዎች የአማራን መከራ ለማራዘም የሚሰሩ የውስጥም የውጭም ባንዳዎች በዝርዝር ተለይተው የተያዙ በመሆናቸው ወሳኙ ሁሉን አቀፍ የአማራ ህዝባዊ እምቢተኝነት ከመጀመሩ በፊት በእነዚህ ባንዳዎች ላይ ተገቢውን እርምጃ የሚወሰድ በመሆኑ መላው ህዝባችንም ለዚህ የተቀደሰ ሃሳብ ተባባሪ እንዲሆን እንዲሁም በአራቱም የአማራ አፅመ እርስቶች (ጎጃም ፣ሸዋ ፣ወሎ እና ጎንደር ) ተጠናክሮ የቀጠለው የአማራ ህዝብ ትግል በተናበበ ሁኔታ እንዲቀጥል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ።
ህልውናችን በክንዳችን !!!
የአማራ ህዝባዊ ኮሚቴ!!
ሰኔ 19/2015 ዓ.ም