09/10/2025
ድርጅታችን ኮምፖስ ፕሮፐርቲስ ታሪካዊ የሆነ ስምምነት ከጎህ ቤቶች ባንክ ጋር ተፈራርሟል።
በስምምነቱ ቤት ፈላጊዎች በግል የባንክ አካውንታቸው ገንዘባቸውን ቆጥበው የሚፈልጉት አይነት ቤት ተሰርቶላቸው የሚወስዱበት አዲስ ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል ።
በሪል ስቴት እና የተለያዩ ትላልቅ የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክቶች የረጅም ጊዜ ልምድ እና ታማኝነት ያለው ድርጅታችን ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ ከጎህ ቤቶች ባንክ ጋር በጋራ ተግባራዊ ያደረግነው በአይነቱ አዲስ የሆነ የቤት ግንባታ ፕሮጀክት ማክሰኞ መስከረም 27 ይፋ ተደርጓል።
ይህ አዲስ ፕሮጀክት በሌላው አለም የሪል ስቴት ዘርፍ በስፋት ስራ ላይ የዋለ ሲሆን በሃገራችን ግን እስካሁን ያልተተገበረ አሰራር መሆኑን የኮምፓስ ፕሮፐርቲስ የስራ ሃላፊዎች ገልፀዋል።
ይህ አዲስ ፕሮጀክት፤ ቤት መግዛት የሚፈልግ ግለሰብ በቅድሚያ 500 ሺ ብር ተቀማጭ በማስገባትና በሚፈልገው የቤት ካሬ መሰረት በየወሩ በራሱ ስም በጎህ ቤቶች ባንክ ደብተር ከፍቶ መቆጠብ የሚጠበቅበት ሲሆን ለቁጠባው 15% ወለድ ይታሰብለታል።
በዚህ ሂደት ውስጥ ግን ገንዘቡ በራሱ በግለሰቡ አካውንት የሚቀመጥ እንጂ ወደ ኮምፓስም ሆነ ወደ ጎህ አካውንት የሚገባ ምንም አይነት ገንዘብ አይኖርም ተብሏል።
በተጨማሪም ቤት ፈላጊው በሚፈልገው የጊዜ ገደብ ቤቱ ተጠናቆ መረከብ የሚችል ሲሆን ካርታ ሲረከብ ብቻ ገንዘቡን ከራሱ የቁጠባ ሂሳብ ወደ ቤት ገንቢው ያስተላልፋል። ቤት ገዢዉ የቆጠበውን ገንዘብ ማውጣት ከፈለገ ደግሞ ለባንኩ ቀድሞ በማሳወቅ ማዉጣት እንዲችል አሠራር ተቀምጧል:: በተጨማሪም ለዚህ አገልግሎት ምንም አይነት የአገልግሎት ክፍያ አይጠየቅበትም ተብሏል።
ይህ የስምምነት ፊርማ ከተማው ላይ ከሪል ስቴት ጋር ተያይዞ በተደጋጋሚ የሚሰማውን ቅሬታ እና ችግር በእጅጉ ይቀርፈዋል የሚል እምነት እንዳላቸውም ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ እና ጎህ ቤቶች ባንክ ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ታሪክ ቀያሪ የሆነ "ታላቅ የምስራች" ይዘን መተናል።
🧭 Compass Properties🧭
0092 352 6961 0942369553