10/06/2026
የሪል ስቴት ኩባንያዎች ቤት የሚሸጡበትን አማካይ ዋጋ መተመን የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ መሆኑ ተነገረ
: የሪል ስቴት ኩባንያዎች ለቤት ግንባታ ወጪ ያደረጉትን መሠረት ያደረገ አማካይ የሽያጭ የዋጋ ተመን እንዲኖር የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ መሆኑን፣ የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማኅበር አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማኅበር ዋና ጸሐፊ ዝናቡ ተበጀ (ኢንጂነር) እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ የሚገኙ ሪል ስቴቶች ቤት የሚሸጡበት አማካይ ዋጋ ተመን እንዲኖር የሚያስችል ጥናት እየተደረገ ነው፡፡ ጥናቱ አንድ ቤት ከተቆረጠለት ዋጋ በታች መሥራት እንደማይቻል፣ ዋጋው አነሰ ብቻ በሚል ገዥዎች በመወሰን ተጎጂ የሚሆኑበትን አካሄድ ለመቀየር እንደሚረዳ ተናግረዋል።
በገበያው ውስጥ ከ50 ሺሕ እስከ 400,000 ሺሕ ብር በካሬ ሜትር የሚሸጡ የሪል ስቴት ኩባንያዎች መኖራቸውን፣ በተለይ መነሻው ዋጋው አንድ የሪል ስቴት ኩባንያን ያሠራል ወይ? የማርኬቲንግ፣ የፋይናንስ፣ የግብር፣ እንዲሁም የመሬት ክፍያን ጨምሮ ግንባታው በአጠቃላይ የሚፈጀው ወጪ (Total Development Cost) መሠረት ያደረገ እንዲሆን ጥናቱ እንደሚያስችል ተናግረዋል። በጥናቱ መሠረት በከፊልና ሙሉ ለሙሉ ያለቁ ቤቶች ዋጋቸው ስንት ይሁን የሚል አማካይ የዋጋ ተመን እንደሚቆረጥ አስረድተዋል።
ጥናቱን ማድረግ ያስፈለገበትን ምክንያት ሲያስረዱ አንዳንድ የሪል ስቴት ኩባንያዎች ሌሎች ኩባንያዎች የሚሸጡበት ዋጋ ተፅዕኖ አሳድሮባቸው ተመሳሳይ ዋጋ የሚያስከፍሉበት አሠራር መኖሩን፣ ማኅበሩ ከደረሰበት ግንዛቤ መነሻ በማድረግ መሆኑን ዝናቡ (ኢንጂነር) ገልጸዋል።
2A Homes, 2ኤ ሆምስ