2A Homes, 2ኤ ሆምስ

2A Homes, 2ኤ ሆምስ ( Your trusted partner )
👉 +251-928-428184

This is 2A Homes, 2ኤ ሆምስ official page, experienced temer real estate sales professional with 5 years of experience serving clients in the Addis Ababa, Ethiopia.
ንብረት ከመግዛትዎ በፊት እኛን ያማክሩ ፤ በታማኝነት እናገለግላለን.

በአዲስ አበባ የ2019 ዓ.ም የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ ተወሰነ ፤ የውል ምዝገባም ከ ዛሬ ሐምሌ 1 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫ...
08/07/2026

በአዲስ አበባ የ2019 ዓ.ም የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ ተወሰነ ፤ የውል ምዝገባም ከ ዛሬ ሐምሌ 1 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት ታላቅ እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል።

ከዚህ ቀደም በወጣው የቤት ኪራይ ቁጥጥር አዋጅ መሠረት፣ ለ2019 በጀት ዓመት የሚተገበረው ፍትሐዊ የቤት ኪራይ ዓመታዊ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መጽደቁን የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።

ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ አዲስ የውል እድሳት ምዝገባ ከዛሬ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት በይፋ መተግበር ይጀምራል።

ቢሮው እንዳመለከተው ፣ ይህ የዋጋ ማስተካከያ ውሳኔ በዘፈቀደ የተወሰነ ሳይሆን በከተማዋ ሰፊ ሳይንሳዊ ጥናት ተካሂዶ የነዋሪውን እውነተኛ የመክፈል አቅም ባገናዘበ መልኩ የተዘጋጀ ነው።

ይህ አሰራር በአንድ በኩል አከራዮች ወቅቱንና የኢኮኖሚ ሁኔታውን ያገናዘበ ፍትሐዊ ገቢ እንዲያገኙ የሚያረጋግጥ ሲሆን ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ተከራዮች ከገቢያቸው ጋር የተመጣጠነ ኪራይ በመክፈል ከተደጋጋሚ መፈናቀልና ከስነ-ልቦና ስጋት ድነው የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ ያደርጋል።

ውሳኔው በከተማዋ ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ ረገድ የጎላ ማህበራዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ እና መልካም አስተዳደር ፋይዳዎች እንዳሉት ቢሮው አረጋግጧል።


Source : የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

"Sandstorm S24 ከቤንዚን ወደ ኤሌክትሪክ ተለወጠ" በቤንዚን የሚንቀሳቀስ የ ' Sandstorm S24 ' ፒክአፕ ተሽከርካሪን ወደ ሙሉ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በተሳካ ሁኔታ መቀየሩን የ...
05/07/2026

"Sandstorm S24 ከቤንዚን ወደ ኤሌክትሪክ ተለወጠ"

በቤንዚን የሚንቀሳቀስ የ ' Sandstorm S24 ' ፒክአፕ ተሽከርካሪን ወደ ሙሉ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በተሳካ ሁኔታ መቀየሩን የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የኢንጂነሪንግ ኮሌጅ አሳውቋል።

ፕሮጀክቱ በዩኒቨርሲቲው የአውቶሞቲቭ ኢንጂነሪንግ ተመራማሪዎች የተመራ ሲሆን ተሽከርካሪውን የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ ነው የሰጠው።

ተሽከርካሪው እስከ 400 ኪሎ ሜትር የመንገድ ጉዞ እንደሚያደርግ፣ የአሠራር ወጪን በ88 በመቶ እንደሚቀንስ፣ ዜሮ የጭስ ልቀት እንደሚያስመዘግብ እና የፕሮጀክቱ ወጪ ከ4 እስከ 5 ዓመታት ውስጥ ሊመለስ እንደሚችል ተገልጿል።

በፕሮጀክቱ ፦
👉 70 ኪሎዋት PMSM ኤሌክትሪክ ሞተር፣
👉 65 ኪሎዋት ሰዓት ሊቲየም-አዮን ባትሪ፣
👉 3.3 ኪሎዋት AC/DC ቻርጂንግ ስርዓት እና Regenerative Braking ቴክኖሎጂ መተግበሩ ተመላክቷል።

source : tikva Ethiopia

NEW SITE LAUNCH ALART!!!
04/07/2026

NEW SITE LAUNCH ALART!!!

ንብረት ገዝተው የስም ዝውውር ያላደረጉ ዜጎች በአስቸኳይ እንዲያጠናቅቁ ታዘዘ  | ከሪል እስቴት አልሚዎችም ሆነ ከግለሰቦች በሰነዶች ማረጋገጫ ንብረት ገዝተው፣ እስካሁን ወደ መሬት ተቋማት በ...
02/07/2026

ንብረት ገዝተው የስም ዝውውር ያላደረጉ ዜጎች በአስቸኳይ እንዲያጠናቅቁ ታዘዘ

| ከሪል እስቴት አልሚዎችም ሆነ ከግለሰቦች በሰነዶች ማረጋገጫ ንብረት ገዝተው፣ እስካሁን ወደ መሬት ተቋማት በመቅረብ የስም ዝውውር ያላደረጉ እና የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ (ካርታ) ያልያዙ ባለንብረቶች ሂደቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀረበ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ መኮንን ያኢ ከኤ ኤም ኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ የስመ-ንብረት ዝውውር በወቅቱ አለመደረጉ ንብረት ገዝተው የባለቤትነት ማረጋገጫ ያልያዙ ዜጎችን ለተለያዩ ከፍተኛ ጉዳቶች እና ለአደጋ እየዳረገ ይገኛል።

የስመ-ንብረት ዝውውር የመጨረሻ ግቡ ገዥው አካል ህጋዊ የይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫን እንዲይዝ ማድረግ ቢሆንም፣ በተለያዩ ምክንያቶች ይህንን ሳያደርጉ የቀሩ በርካታ አካላት መኖራቸውን ቢሮው ጠቁሟል።

በመሆኑም ቀደም ባሉ ጊዜያት የመኖሪያ ቤትም ሆነ ማንኛውንም በመሬት ላይ ያረፈ ንብረት ገዝተው የስም ዝውውር ያላደረጉ ባለንብረቶች፣ መብታቸውን ለማስከበርና ለከፋ አደጋ እንዳይጋለጡ ሲባል መንግስት በአስቸኳይ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ ሂደቱን እንዲያጠናቅቁ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።


የቦሌ ኖክ ፓርኪንግ እና ፕላዛ ግንባታ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።የከተማዋን ሁለንተናዊ ለውጥ ዕውን የሚያደርጉ ዘርፈ-ብዙ ፕሮጀክቶችን በላቀ ጥራትና ፍጥነት እያከናወነ የሚገኘው የአዲስ ...
20/06/2026

የቦሌ ኖክ ፓርኪንግ እና ፕላዛ ግንባታ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።

የከተማዋን ሁለንተናዊ ለውጥ ዕውን የሚያደርጉ ዘርፈ-ብዙ ፕሮጀክቶችን በላቀ ጥራትና ፍጥነት እያከናወነ የሚገኘው የአዲስ አበባ ዲዛይንና ግንባታ ስራዎች ቢሮ የመዲናዋን የትራንስፖርት ስርዓት የሚያጎለብቱ ፣ የዕድገት ግስጋሴዋን የሚመጥኑ ፣ የነዋሪዎቿን የከተሜነት ስነ-ልቦናዊ ውቅር የተረዱ እንዲሁም ከቴክኖሎጂ ጋር የተዋደዱ ስማርት ፓርኪንጎችንና ፕላዛዎችን በስፋት በማስገንባት ለአገልግሎት እያበቃ ይገኛል።

ቢሮው እየተገባደደ በሚገኘው በጀት ዓመት አጠናቆ ለሕብረተሰብ አገልግሎት ካበቃቸው በቁጥር የበዙ ስማርት ፓርኪንግ እና ፕላዛዎች በተጨማሪ በቦሌ ፣ በአራዳ እና በየካ ክፍለከተሞች እያስገነባቸው የሚገኙትን ተጨማሪ የፓርኪንግ እና ፕላዛ ግንባታዎች ባጠረ ጊዜ አጠናቆ ወደ አገልግሎት ለማስገባት በልዩ ትኩረት እየሰራ ይገኛል።

ከነኚሁ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነውና በ2,400 ካ.ሜ ቦታ ላይ እየተገነባ የሚገኘው የቦሌ ኖክ ፓርኪንግ እና ፕላዛ ፕሮጀክትም 2 ወለል ባለው ቤዝመንቱ 80 ተሽከርካሪዎችን በስታንዳርድ የማስቆም ዓቅም ያለው ሲሆን በተጨማሪም በግራውንድ ወለሉ በተመሳሳይ ጊዜ 18 ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ የታክሲ ተርሚናልን ጨምሮ 38 ሱቆች ፣ 2 ሬስቶራንቶች ፣ ጁስ ኮርት ፣ ተዝናኖትን የሚያጎናፅፍ ሰፊ የሕዝብ መዝናኛ ስፍራ እንዲሁም የሰርቬላንስ እና የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ቅድመ መከላከል ስርዓቶች የተሟሉለት ነው።

ይህንን ጨምሮ ሌሎቹም መሰል ፕሮጀክቶች የመዲናዋን የተሽከርካሪ ፍሰት ስርዓት ከማዘመናቸው ባሻገር የተቀናጀ አገልግሎት ይሰጡ ዘንድ በተያዘላቸው ውጥን መሰረት ተያያዥ ፋሲሊቲዎችን ያካተቱ በመሆናቸው የስራ ዕድል በመፍጠርና ፋይናንስ በማመንጨት ለሕብረተሰቡ ተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታን የሚያጎናፅፉ ናቸው።

💰 በአዋሬ ቤተመንግስት ጀርባ ከ 10 ሚሊዮን ብር ጀምሮ ባለ 3 መኝታ ዘመናዊ አፓርትመንት ባለቤት ይሁኑ!​✨​አነስተኛ ቅድመ ክፍያ፦ 20% ብቻ ከፍለው የቤቱ ባለቤት ይሁኑ።​✨ያለ ወለድ (...
18/06/2026

💰 በአዋሬ ቤተመንግስት ጀርባ ከ 10 ሚሊዮን ብር ጀምሮ ባለ 3 መኝታ ዘመናዊ አፓርትመንት ባለቤት ይሁኑ!

​✨​አነስተኛ ቅድመ ክፍያ፦ 20% ብቻ ከፍለው የቤቱ ባለቤት ይሁኑ።

​✨ያለ ወለድ (Interest-Free)፦ ቀሪውን 80% ክፍያ በ3 ዓመት ጊዜ ውስጥ ያለምንም ዋጋ ጭማሪ ይክፈሉ።

​✨​ታላቅ ቅናሽ፦ ለሙሉ ክፍያ የ 35% ልዩ ቅናሽ ተጠቃሚ ይሆናሉ።

​📍 ልዩ መገኛ፦
​ቤተመንግስት አቅራቢያ የሚገኝ አስተማማኝና ምቹ ሰፈር።
​ለስራ እና ለትምህርት ቤቶች ቅርብ የሆነ ስትራቴጂካዊ ቦታ።

​✨ቴምር ፕሮፐርቲስ 10ኛ ዓመቱን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው ይህ ልዩ ዕድል፣ በከተማዋ እምብርት እና አስተማማኝ ጥበቃ በሚገኝበት አዋሬ ቤተመንግስት ጀርባ የቅንጦት መኖሪያን ለሚፈልጉ የተዘጋጀ ነው።

​✨ የታላቁ አጋርነት እና የ10ኛ ዓመት ጥቅሞች፦
👇
​ የShebaMiles ስጦታ፦
ቤት ሲገዙ ለዓለም አቀፍ በረራ የሚያገለግሉ ማይልሶችን በስጦታ ያግኙ።

​የነገውን ህልምዎ ዛሬ ያሳኩ!

​📞 ለበለጠ መረጃ: 0928428184
:0940727212

የሪል ስቴት ኩባንያዎች ቤት የሚሸጡበትን አማካይ ዋጋ መተመን የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ መሆኑ ተነገረ  : የሪል ስቴት ኩባንያዎች ለቤት ግንባታ ወጪ ያደረጉትን መሠረት ያደረገ አማካይ የሽ...
10/06/2026

የሪል ስቴት ኩባንያዎች ቤት የሚሸጡበትን አማካይ ዋጋ መተመን የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ መሆኑ ተነገረ

: የሪል ስቴት ኩባንያዎች ለቤት ግንባታ ወጪ ያደረጉትን መሠረት ያደረገ አማካይ የሽያጭ የዋጋ ተመን እንዲኖር የሚያስችል ጥናት እየተካሄደ መሆኑን፣ የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማኅበር አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማኅበር ዋና ጸሐፊ ዝናቡ ተበጀ (ኢንጂነር) እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ የሚገኙ ሪል ስቴቶች ቤት የሚሸጡበት አማካይ ዋጋ ተመን እንዲኖር የሚያስችል ጥናት እየተደረገ ነው፡፡ ጥናቱ አንድ ቤት ከተቆረጠለት ዋጋ በታች መሥራት እንደማይቻል፣ ዋጋው አነሰ ብቻ በሚል ገዥዎች በመወሰን ተጎጂ የሚሆኑበትን አካሄድ ለመቀየር እንደሚረዳ ተናግረዋል።
በገበያው ውስጥ ከ50 ሺሕ እስከ 400,000 ሺሕ ብር በካሬ ሜትር የሚሸጡ የሪል ስቴት ኩባንያዎች መኖራቸውን፣ በተለይ መነሻው ዋጋው አንድ የሪል ስቴት ኩባንያን ያሠራል ወይ? የማርኬቲንግ፣ የፋይናንስ፣ የግብር፣ እንዲሁም የመሬት ክፍያን ጨምሮ ግንባታው በአጠቃላይ የሚፈጀው ወጪ (Total Development Cost) መሠረት ያደረገ እንዲሆን ጥናቱ እንደሚያስችል ተናግረዋል። በጥናቱ መሠረት በከፊልና ሙሉ ለሙሉ ያለቁ ቤቶች ዋጋቸው ስንት ይሁን የሚል አማካይ የዋጋ ተመን እንደሚቆረጥ አስረድተዋል።
ጥናቱን ማድረግ ያስፈለገበትን ምክንያት ሲያስረዱ አንዳንድ የሪል ስቴት ኩባንያዎች ሌሎች ኩባንያዎች የሚሸጡበት ዋጋ ተፅዕኖ አሳድሮባቸው ተመሳሳይ ዋጋ የሚያስከፍሉበት አሠራር መኖሩን፣ ማኅበሩ ከደረሰበት ግንዛቤ መነሻ በማድረግ መሆኑን ዝናቡ (ኢንጂነር) ገልጸዋል።
2A Homes, 2ኤ ሆምስ

11/05/2026

የታክስ አይነቶችና የማሳወቂያ ጊዜያት


👉ከራስ ገቢ ላይ የሚቀንስ በየ3 ወሩ፣
👉ድርጅቶች በየወሩ፡፡


👉ደረጃ “ሀ” ከሐምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30፤
👉ደረጃ “ለ” ከሐምሌ 1 እስከ ጳጉሜን 5/6፤
👉ደረጃ “ሐ” ከሐምሌ 1 ቀን እስከ ሐምሌ 30፤

#በሰንጠረዥ “መ” ሌሎች ገቢዎች ምድብ ስር የሚመደቡት የገቢ አይነቶች
👉ሮያሊቲ፣
👉የትርፍ ድርሻ፣
👉ወለድ፣
👉ከእድል ሙከራ የሚገኝ ገቢ፣
👉የቴክኒክ እና ሰራ አመራር ክፍያ፣
👉ግብሩ ተቀናሽ ካልተደረገ በስተቀር ገቢውን ያስገኘው ግብይት ከተደረገበት ቀን
ጀምሮ ባሉት ሁለት ወራት፡፡


👉በሀገር ውስጥ ከሚፈጽሙ ክፍያዎች ላይ በወሩ ውስጥ ቀንሶ ቀሪ ያደረገውን
አጠቃላይ ግብር ከወሩ የመጨረሻ ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት፣
👉ከውጭ ሀገር በሚገቡ እቃዎች ላይ እቃዉ በገባበት ጊዜ ተጨማሪ እሴት ታክስን
በሚመለከት ግብይቱ ከተካሄደበት ቀን መጨረሻ ባሉት 30 ቀናት ውስጥ፡፡


👉ደረጃ “ሀ” በየወሩ፣
👉ደረጃ “ለ” በየሶስት ወሩ፣
👉ደረጃ “ሐ” በበጀት ዓመቱ መጨረሻ፡፡


👉ከአምራቹ ፋብሪካ በሚወጡበት ጊዜ የሚከፈለው በየወሩ፤
👉ፋብሪካ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋሉ ዕቃዎች ጥቅም ላይ በዋሉበት ጊዜ፤የሚከፈለው
በየወሩ፡፡

2A Homes, 2ኤ ሆምስ

 , ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ3.3 ቢልየን ብር ወጭ የባህርዳሩን  ጣና ሆቴል በአዲስ  መልክ ሊገነባው ነው። ግሩፑ ይህንን ያስታወቀው ዛሬ በባህር ዳር ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ባ...
04/05/2026

,
ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ3.3 ቢልየን ብር ወጭ የባህርዳሩን ጣና ሆቴል በአዲስ መልክ ሊገነባው ነው።

ግሩፑ ይህንን ያስታወቀው ዛሬ በባህር ዳር ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ባደረገው ስብሰባ ነው ::

በፎርፖይንት ባይ ሸራተን ማርዮት ኢንተርናሽናል ደረጃ በአዲስ መልክ የሚገነባው ጣና ሆቴል 120 ዘመናዊ የመኝታ ክፍሎች :የስብሰባ አዳራሾች ፡ ዘመናዊ የ መዋኛ ገንዳ:
ጅምና ሰፓ ይኖሩታል ተብሏል ::

ግንባታው በ18 ወራት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ግምት ተሰጥቶታል ::

Source : zahebesha

ከሁለት አባት ከአንድ እናት የተወለዱ መንትዮች ​  Homes I ላቪኒያ እና ሚሼል ኦስቦርን የተባሉ መንታ ልጆች በተደረገላቸው የዲኤንኤ ምርመራ የተለያዩ አባቶች እንዳሏቸው ተረጋገጠ። ይህ ...
03/05/2026

ከሁለት አባት ከአንድ እናት የተወለዱ መንትዮች

​ Homes I ላቪኒያ እና ሚሼል ኦስቦርን የተባሉ መንታ ልጆች በተደረገላቸው የዲኤንኤ ምርመራ የተለያዩ አባቶች እንዳሏቸው ተረጋገጠ። ይህ በሕክምናው ዓለም "Heteropaternal Superfecundation" ተብሎ የሚጠራው ብርቅዬ ክስተት፣ በዩናይትድ ኪንግደም በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰነድ የተመዘገበ የመጀመሪያው ጉዳይ ሆኗል።

​በአሁኑ ወቅት ዕድሜያቸው 49 ዓመት የሆኑት እነዚህ መንታ እህቶች፣ ሚስጥሩ ሊታወቅ የቻለው ሚሼል ኦስቦርን እ.ኤ.አ. በ2022 ባደረገችው የDNA ምርመራ ነው። ምርመራው ሁለቱም እህቶች በአንድ ማህፀን አብረው ቢያድጉና በደቂቃዎች ልዩነት ቢወለዱም፣ ባዮሎጂካዊ አባቶቻቸው ግን የተለያዩ መሆናቸውን አረጋግጧል።

​ክስተቱ ሊከሰት የቻለው እናታቸው በአንድ የወር አበባ ዑደት ውስጥ ከአንድ በላይ እንቁላል አፍርታ፣ በተለያዩ የግብረ-ሥጋ ግንኙነቶች አማካኝነት በተለያዩ ወንዶች ዘር እንዲዳበሩ በመደረጉ እንደሆነ ተገልጿል። በዓለም አቀፍ ደረጃ እስካሁን የተመዘገቡት እንዲህ ዓይነት ክስተቶች ከ20 የማይበልጡ በመሆናቸው ጉዳዩን እጅግ አስገራሚ አድርጎታል ይላል የቢቢሲ ዘገባ።

​ላቪኒያ እና ሚሼል አስቸጋሪ የልጅነት ጊዜን አብረው ያሳለፉ ሲሆን፣ ውጤቱ መጀመሪያ ላይ አስደንጋጭ ቢሆንባቸውም አሁንም ያላቸው "የመንትያነት" ትስስር የማይበጠስ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ሁለቱም እህቶች የየራሳቸውን እውነተኛ አባቶች ማግኘት የቻሉ ሲሆን፣ ላቪኒያ ከአባቷ ከአርተር ጋር የጠበቀ ግንኙነት መመሥረት ችላለች።

Source: Fastmereja.com

Address

Sarbet
Addis Ababa
SARBETTOKERAROAD,WOLDRMARIEMBUILDING,ADDISABABA,

Telephone

+251928428184

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when 2A Homes, 2ኤ ሆምስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share