13/10/2021
❗ ⤵️
➣ የተጣራ ገቢ ደመወዝ= ሙሉ ደመወዝ - ((ሙሉ ደመወዝ*ደመወዙ የተጣለበት ታክስ %- የግብር %ቱ ያረፈበት ተቀናሽ ብር) + (ሙሉ ደመወዝ*ጡረታ ግብር (7%)))
ለምሳሌ የእኔ ደመወዝ 6000 ብር ቢሆን
🔧 ሙሉ ደመወዝ =6000
🔧 ደመወዙ የተጣለበት ታክስ= 25% (0.25)
🔧 ደመወዙ ያረፈበት ተቀናሽ ብር = 565
🔧 ጡረታ ግብር = 7% (0.07) ለሁሉም ደመወዝ ስኬል ተመሳሳይ ነው ።
ስለዚ፦
የተጣራ ደመወዝ = 6000-((6000*0.25 -565)+( 0.07*6000))
= 6000-1355
➜ የተጣራ ደመወዝ = 4645 (ይህ በኪስ የሚደርስ ደመወዝ ነው) ።
➲ በተጨማሪም ለፖለቲካ ድርጅት እገዛ፣ ለኤች አይ ቪ ህሙማን እርዳታና ለህፃናት ማሳደጊያ በየወሩ ከደመወዝ ላይ የሚቆረጥበት ሁኔታ ካለ ከዚህ በታች የሆነ የተጣራ ገቢ ደመወዝ የሚደርስ ይሆናል።
ላልገባችሁ ያልገባችሁን ነገር Comment ላይ መጠየቅ ትችላላችሁ።
✅ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር
ከግብር ነፃ ከሆነው በስተቀር ቀጣሪው ለተቀጣሪው በሚከፍለው ማንኛውም የገንዘብ መጠን ላይ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር ይከፈልበታል።
✅ ቀጣሪ ማለት ተቀጣሪን የቀጠረ ወይም ለተቀጣሪው ደመወዝ የሚከፍል ሰው ወይም ድርጅት ነው።
✅ ተቀጣሪ ማለት ደግሞ ራሱን ችሎ የሚሰራን የስራ ተቋራጭ ሳይጨምር በቀጣሪው መሪነትና ቁጥጥር ስር ሁኖ አገልግሎት ለመስጠት በቋሚነት ወይም በጊዜያዊነት የተቀጠረ ግለሰብ ማለት ነው።
✅ ተቀጣሪ የድርጅት ዳይሬክተር ወይም በድርጅት አመራር ውስጥ ኃላፊነት የተሰጠውን ሌላ ሰው እንዲሁም ተሿሚንና የህዝብ ተመራጭን ጨምሮ የመንግስት ስራ ኃላፊን ያጠቃልላል።
✅ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ የሚከተሉትን ያጠቃልላል
🔶 ከሰራተኛው ቅጥር ጋር በተያያዘ ሰራተኛው የተቀበለው ደመወዝ ምንዳ፣ አበል፣ ጉርሻ፣ ኮሚሽን እና የመልካም ስራ አፈጻፀም ማበረታቻ ስጦታ ወይም ሌላ የአገልግሎት ክፍያ፣
🔶 ሰራተኛው ከቅጥር ውሉ ጋር በተያያዘ በዓይነት የሚቀበለው ማንኛውም ጥቅማጥቅም ዋጋ፣
🔶 ተቀጣሪው ከስራ ሲቀነስ ወይም ከስራ ሲለቅ ወይም
ስራን እንዲለቅ ለመማግባባት የሚከፈል ገንዘብን
ጨምሮ የስራ ውል በመቋረጡ ምክንያት በፈቃደኝነት ፣
በስምምነት ወይም በዳኝነት ውሳኔ መሠረት የተቀበለው
ማንኛውም የገንዘብ መጠን።
✅ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር የማስከፈያ ምጣኔዎች
🔶 ቀጣሪው ለተቀጣሪው ከተከፈለው የገንዘብ መጠን ላይ ግብሩን ሳይቀንስ ከራሱ ግብሩን የከፈለ እንደሆነ የተከፈለው ግብር በተቀጣሪው ደመቀዝ ተደምሮ ግብሩ ይሰላል።
ሠንጠረዥ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ላይ የሚከፈል ግብር በመቶኛ ከመቀጠር የሚገኙ ገቢዎች ከግብር ነፃ ስለመሆናቸው የሚከተሉት ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ላይ ከሚከፈል ግብር ነፃ ይሆናሉ።
1. ሰራተኛው ሲታመም አሰሪው ለሰራተኛው የሕክምና
አገልግሎት የከፈለለት ገንዘብ፣
2. በስራ ውል መሠረት ለሰራተኛው የሚከፈል የመጓጓዛ
(ትራንስፖርት) አበል፣
3. በስራ ቦታው ወይም በስራ ሁኔታው አስቸጋሪንት
ምክንያት ለሰራተኛው የሚከፈል አበል፣
4. ሰራተኛው ከመደበኛ ስራው ውጪ ስራውን
ለማከናወን ሲንቀሳቀስ የሚከፈለው የመጓጓዛ ወጪ እና
የወሎ አበል፣
5. የመጓጓዛ ወጪው በቅጥር ውሉ መሠረት የተከፈለ
ከሆነ ከስራ ቦታው ውጪ ተመልምሎ ለተቀጠረ ሰራተኛ
ወደ ስራው ሲመጣ ወይም ስራውን አጠናቆ ሲመለስ
የሚከፈለው (የመጓጓዛ ) ወጪ ፣ እንዲሁም የውጭ
ሀገር ሰራተኞች ከሀገራቸው ሲመጡና ወደ ሀገራቸው
ሲመለሱ የሚከፈል የመጓጓዛ ወጪ፣
6. የማዕድን ማውጣት፣ “የማኑፋክቸሪንግ” እና
የግብር እና ንግድ ስራ የሚሰራ ቀጣሪ ለተቀጣሪው በነፃ
የሚያደርገው ምግብና መጠጥ፣
7. የኢትዮዽያ መንግስት በውጭ አገር ለሚመድባቸው
ሰራተኘፐቹ የሚከፈል አበል፣
8. የመንግስት የልማት ድርጅቶች ፣ ምስሪያ ቤቶች
የቦርድ አባል፣ ፀሐፊ፣ የፌዴራልና የክልል መንግስታት
ወይም የከተማ አስተዳደሮች በሚያቋቋሟቸው የጥናት
ቡድኖች አባል ወይም ፀሐፊ በመሆን የሚከፈል አበል፣
9. ለሰራተኛው ጥቅም ተብሎ ከተቀጣሪው የወር
ደመወዝ 15% (አስራ አምስት በመቶ) ባልበለጠ
መጠን በየወሩ በቀጣሪው የሚዋጣ የጡረታ መዋጮ
ወይም የ”ፕሮቪደንት ፈንድ” ፣
10. በመንግስት ሰራተኞች የጡረታ አዋጅ እና በግል
ድርጅቶች ሰራተኞች የጡረታ አዋጅ ከግብር ነፃ የተደረገ
የጡረታ ገቢ፣
11. የኢትዮያ የፌዴራል፣ የክልል፣ የአካባቢ መንግስታት
ወይም የኢትዮዽያ ብሔራዊ ባንክ ከመደበኛ
ስራዎቻቸው በተያያዘ የሚያገኙት ገቢ፣
12. በዓለም አቀፍ ስምምነት መሠረት ከግብር ነፃ
የሆነ ገቢ፣ በኢትዮዽያ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት በተደረ
ስምምነት መሠረት ማናቸውም ገቢ ከግብር ነፃ
የሚሆነው የሚከተሉት ሁኔታዎች ተሟልተው ሲገኙ
ነው;-
ስምምነቱ የተደረገው ለመንግስት የገንዘብ፣ የቴክኒክ፣
ሰብዓዊ ወይም አስተዳደራዊ እርዳታ ለማቅረብ የሆነ
እንደሆነ፣ ከግብር ነፃ ማድረግ የሚያስችለውን አንቀፅ
በሚመለከት የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ
መስማማቱን በጽሁፍ ሲገልጽ፣
1. በማንኛውም መስክ ለላቀ የስራ ክንውን የሚሰጥ
ሽልማት፣
2. በተቀባዩ ላይ በደረሰ ጉዳት ወይም በሌላ ሰው ሞት
ምክንያት የሚከፈል ካሳ፣
3. በስጦታ ወይም በውርስ የሚገኝ ጥሬ ገንዘብ ወይም
ሀብት፣
4. በትምህርት ተቋም ውስጥ ትምህርት በነፃ
ለመከታተል የሚፈፀም ክፍያ፣
5. ለቀለብ ወይም ለሕፃናት ድጋፍ የሚሰጡ ክፍያዎች፣
6. ድርጅቱ ከተቋቋመበት ዓላማ ጋር የማይገናኝ የንግድ
ስራ ገቢን ሳይጨምር ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት
የሚያገኘው ገቢ፣
7. ገንዘብ በሚቆጠርበት ጊዜ ለሚደርሰው ጉድለት
ማካካሻ በሚሆን መጠን ብቻ ቀጣሪው ለተቀጣሪው
የሚከፍለው እና ለዚሁ ዓላማ መዋሉ የተረጋገጠ የጥሬ
ገንዘብ ማካካሻ ክፍያ፣
8. በኢትዮዽያ በሚሰራበት ሕግ መሠረት በተለይ ከገቢ
ግብር ነፃ የተደረ ገቢ፣
9. ለመኖሪያ ቤት ውስጥ ሰራተኞች የሚከፈል
ደመወዝ፣
10. በነዳጅ ስራ ለይ የተሰማሩ ስራ ተቋራጭ ለንዑስ
ስራ ተቋ
📌 ኃላፊነቱ የተወስነ የግል ማህበር እና አክሲዮን ማህበር ያላቸውን መሠረታዊ ልዩነት በዝርዝር የሚያብራራ ጠቃሚ መረጃ ጠበቃ ሳሙኤል ግርማ 0911 190 299 ቴሌግራም፡ ht...