Sibaye-Korke YOUTH League"

Sibaye-Korke YOUTH League" LIVE TO TOMORROW

አጨራረስ ታየኝ
22/08/2026

አጨራረስ ታየኝ

በቁጥጥር ስር ውለዋል ግን ደግሞ ልጆች ናቸው ተብለው ከተለቀቁ??
17/08/2026

በቁጥጥር ስር ውለዋል ግን ደግሞ ልጆች ናቸው ተብለው ከተለቀቁ??

የህሊና ወ*ንጀል ነው። ይኼ ምግብ ሳይሆን የሕይወት አድን መድሐኒት ነው። ሰዎች ሳያዉቁ ገዝተው ሊመገቡ ይችላሉ። አንዳንዴም ቤተሰብ ለታመመችዋ ልጅ የታዘዘውን ሸጠው ለቤተሰብ ቀለብ የሚገዙ ...
03/08/2026

የህሊና ወ*ንጀል ነው።

ይኼ ምግብ ሳይሆን የሕይወት አድን መድሐኒት ነው። ሰዎች ሳያዉቁ ገዝተው ሊመገቡ ይችላሉ። አንዳንዴም ቤተሰብ ለታመመችዋ ልጅ የታዘዘውን ሸጠው ለቤተሰብ ቀለብ የሚገዙ አሉ። በሞ*ት አፋፍ ላይ ካለ ህፃን ነጥቆ እንደመብላት ነው።

በተለይ ክብደት ለመጨመር እየተባለ ለቅንጦት ከተራበች ነፍስ እየቀሙ እንደሆነ ይወቁ። ለጤናማ ሰው ምናልባትም ለጤና አ*ደገኛ ሊሆን ይችላል ምክንያቱም ምግብ ሳይሆን የምግብ እጥረት መድሐኒት ስለሆነ ነው። አይግዙ፤ አይሽጡ። ለታመሙት ብቻ እናውለው።

 ይህ ወጣት የምጽፈው አጀንዳ ተሰቶት የቡድን ፖለቲካ እንዲቀጥልና በጎራ እንዲከፋፈሉ የሚቀሰቅስ ነው:: ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አይጣፍጥም እኛ የወላይታ ወጣቶች ችግር ካለ እርስበርስ እንመካከራ...
23/07/2026


ይህ ወጣት የምጽፈው አጀንዳ ተሰቶት የቡድን ፖለቲካ እንዲቀጥልና በጎራ እንዲከፋፈሉ የሚቀሰቅስ ነው:: ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አይጣፍጥም እኛ የወላይታ ወጣቶች ችግር ካለ እርስበርስ እንመካከራለን፣ ሲኒየር ፖለቲከኞችን እናከብራን እንጂ አናንቋሽሽም፣ ከፍ ዝቅ አናደርግም፣ ለባዳ አሳልፈን አንሰጥም:: ወጣት ነዋይ የአንተን ፖስትና አጀንዳ ሳናውቅ ቀርተን አይደለም አቶ ገብረመስቀል ጫላም ሆነ ተስፋዬ ይገዙ፣ ዶ/ር ቦጋለ ቦሸም ሆነ ዶ/ር እንዳልካቸው፣ ዳጋቶ ኩምቤም ሆነ እዚም እዛም የሚሰካኩ አመራሮች አንድ መሆናቸው አይቀርም:: ስለሆነም የነገ አገር ተረካቢ ወጣት ነክና በጎራ የሚከፋፍል ትርክት ተወውና አንድ ለማድረግ የበኩልህን ተወጣ::
ለወላይታ አንድነት እንትጋ!

ዛፍ ቆራጩ በአንድ ድርጅት ውስጥ ተቀጠረ።  ክፍያው የሚፈፀምለት በቆረጠው የዛፍ ብዛት ነው። ታድያ በመጀመሪያው ቀን 18 ዛፎችን በመቁረጥ ከፍተኛ ውጤት አሳየ። አሰሪውም በጣም አደነቀው። በ...
18/07/2026

ዛፍ ቆራጩ በአንድ ድርጅት ውስጥ ተቀጠረ። ክፍያው የሚፈፀምለት በቆረጠው የዛፍ ብዛት ነው። ታድያ በመጀመሪያው ቀን 18 ዛፎችን በመቁረጥ ከፍተኛ ውጤት አሳየ። አሰሪውም በጣም አደነቀው። በቀጣዮቹ ቀናት ግን የበለጠ ውጤት ለማምጣት ሰዓት እየጨመረና ያለ እረፍት እየለፋ ቢሰራም፣ የቆረጣቸው ዛፎች ቁጥር ወደ 14፣ ከዚያም ወደ 9 እያለ በከፍተኛ ሁኔታ ቀነሰ። ዛፍ ቆራጩ ጉልበቱ የደከመ መስሎት ተጨነቀ።..
በመጨረሻም ስራውን እንዳያጣ በመፍራት ወደ አሰሪው ሄዶ "በሙሉ ኃይሌ እየሰራሁ ለምን ውጤቴ እንደቀነሰ አላውቅም።" ሲል አማረረ። ..
አሰሪውም "ለመሆኑ መጥረቢያህን ለመጨረሻ ጊዜ የሳልከው መቼ ነው?" አለው። ዛፍ ቆራጩም "ዛፍ በመቁረጥ ተጠምጄ ስለነበር መጥረቢያዬን ለመሳል ጨርሶ ጊዜ አልነበረኝም።"አለው።..
በህይወት ውስጥ ያለ እረፍትና ያለ ስልት ጠንክሮ ከመልፋት በላይ፣ ቆም ብሎ ራስን ማደስና እውቀትን ወይም ክህሎትን ማሳል አስፈላጊ ነው።

 #የመጨረሻው ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ፤ ኢትዮጵያ ከ ዛምቢያየኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚደረገው የዓለም...
12/07/2026

#የመጨረሻው
ከ17 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ፤ ኢትዮጵያ ከ ዛምቢያ

የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚደረገው የዓለም ዋንጫ ለማለፍ፥ ዛሬ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ከዛምቢያ ጋር ወሳኝና ታሪካዊ የመልስ ጨዋታውን ያደርጋል።

​የመጀመሪያውን ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ ጠባብ ውጤት የተሸነፉት ሉሲዎቹ፣ ታሪክ ለመሥራትና በደጋፊያቸው ፊት ድልን ለመቀዳጀት በቁጭትና በከፍተኛ ተነሳሽነት ላይ ይገኛሉ።

ቡድኑ ወደ ዓለም ዋንጫው መድረክ ለመሸጋገር ዛሬ በሚያደርገው ጨዋታ ዛምቢያን በድምር ውጤት መብለጥ የሚኖርበት ሲሆን፣ ለዚህም በጨዋታው አንድ እና ከዚያ በላይ ግብ አስቆጥሮ ማሸነፍ ይጠበቅበታል።

​ይህንን ወሳኝ ፍልሚያ በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ራውዳ አሊ፣ በልጆቻቸው ላይ ሙሉ እምነት እንዳላቸውና ቡድኑ ታሪክ ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

አሰልጣኝ ራውዳ በዛምቢያ ከነበረው የመጀመሪያ ጨዋታ በኋላ ተጫዋቾቻቸው የተሻለ ነገር ባለማድረጋቸው ከፍተኛ ቁጭትና ስሜት ውስጥ እንደነበሩ አስታውሰው፣ "ልጆቻችን አቅማቸውን አውጥተው በመጫወት የተሻለ ነገር ለማሳየት ፍላጎት ስለነበራቸው ይህንን ዛሬ በመልሱ ጨዋታ በተግባር ያሳዩናል" ብለዋል።

አሰልጣኟ አክለውም የኢትዮጵያ ህዝብ እግር ኳስ ወዳድ መሆኑን በመጥቀስ፣ "ቀሪዋን 90 ደቂቃ በስታዲየም ተገኝታችሁ ድጋፍ ስጡን" ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

​የቡድኑ አምበል ምህረት ወሰኑ በበኩሏ፣ በዛምቢያ በደረሰባቸው የ2 ለ 1 ሽንፈት መቆጨታቸውን በማመን፣ "በእልህና በቁጭት በሀገራችን እና በደጋፊያችን ፊት ውጤት ይዘን ለመውጣት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነን" ስትል የቡድኑን የአሸናፊነት ስሜት ገልጻለች።

በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ዓለም ዋንጫ ለማለፍ የምትጫወተው ኢትዮጵያ፤ ዛሬ ቀን 9 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የምታደርገው ጨዋታ በመላው እግር ኳስ ወዳድ ቤተሰብ ዘንድ ከፍተኛ ጉጉትን ፈጥሯል።



ይገምቱ ይሸለሙ
11/07/2026

ይገምቱ ይሸለሙ

🇪🇹  ! #⚽️በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ የመጨረሻ ዙር ማጣርያ የመጀመርያ ጨዋታ ኢትዮጵያ ዛሬ ከሜዳዋ ውጪ ዛምቢያን ትገጥማለች።ጨዋታው ከቀኑ 10፡00 ላይ በንዶላ ሌቪ...
04/07/2026

🇪🇹 ! #⚽️

በ2026 ከ17 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም ዋንጫ የመጨረሻ ዙር ማጣርያ የመጀመርያ ጨዋታ ኢትዮጵያ ዛሬ ከሜዳዋ ውጪ ዛምቢያን ትገጥማለች።

ጨዋታው ከቀኑ 10፡00 ላይ በንዶላ ሌቪ ምዋናዋሳ ስታዲየም ሲካሄድ በጨዋታው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አረንጓዴ ማልያ፣ ቢጫ ቁምጣ፣ ቀይ ካሶተኒ ለብሰው ወደ ሜዳ የሚገቡ ይሆናል።

ድል ለኢትዮጵያ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹

የ2018 ዓ.ም የበጎ ሥራ ጅማሬ
03/07/2026

የ2018 ዓ.ም የበጎ ሥራ ጅማሬ

Address

Wolaita
Boditi
143

Telephone

+251935976056

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sibaye-Korke YOUTH League" posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sibaye-Korke YOUTH League":

Shortcuts

Share

Category