12/08/2022
የዳባት ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት በ2015 ዓ.ም በጀት በሀምሌ ወር ከ5.7 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ፡፡
####################################x
በ2015 ዓ.ም በጀት ዓመት ብር 69,792,281 ለመሰብሰብ አቅዶ በሀምሌ ወር ውስጥ ብር 5,751,061.52 ገቢ መሰብሰብ ተችሏል፡፡ አፈፃፀሙም ከአመቱ አኳያ 8.24% ሲሆን ከአለፈዉ አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 718,352.76 ብር ወይም 1% እድገት አለዉ፡፡ በ2014 ዓ.ም ተመሳሳይ ወቅት የተሰበሰበ ብር 5,032,708.76 ሲሆን በዚህ አመት ተመሳሳይ ወቅት የተሰበሰበ ብር 5,751,061.52 ነዉ፡፡
የተቋሙ የመፈፀም አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ እቅዱ ከ57.2 ሚሊዮን ወደ 69.7 ሚሊዮን አድጓል፡፡ ገቢው የሚሰበሰበውም ከመንግስት ተቀጣሪዎች የስራ ግብር፣ ከግል ድርጅት ተቀጣሪዎች የስራ ግብር፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከተርን ኦቨር ታከስ፣ ከንግድ ትርፍ ግብር እና ከሌሎች ልዩ ልዩ ገቢዎች ነው፡፡