08/12/2022
በጌምድር ሞል አፖርትመንት እና ሪልስቴት በ127 አባላት በጎንደር ከተማ ተወላጆች የተመሰረተ ሲሆን የጎንደር ከተማ የቀደምትነት የነገስታት ዘመን የአፍሪካ መናገሻነት ክብሯን ለማስመለስ የከተማውን እድገት ከፍ ለማድረግ በህንጻ ግንባታና በሪልስቴት ስራ የከተማውን ገጽታ ለመቀየር በሚንቀሳቀሱ ሀገር ወዳድ ነዋሪዎች የተቋቋመ በግንባታና በተግባር ላይ የሚገኝ ማህበር ሲሆን ከብዙ ውጣውረዶች በኃላ በሁለት እግሩ በመቆም የታሰበውን የጎንደር ከተማ የገጽታ ግንባታ በማሳለጥ ላይ የሚገኝ የከተማው ግንባር ቀደም ማህበር ነው ።
በጌምድር አፖርትመንት ሞል እና ሪልስቴት በጎንደር ከተማ በተለያዩ የልማትና የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ቀድሞ በመድረስ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ የሚታወቅ ነው በህልውና ጦርነት በኮረና እንዲሁም በተለያዩ የማህበረሰብ አገልግሎቶች ዙሪያ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደረገ ሀገር ወዳድ ማህበር ነው።