Kofale youth league

Kofale youth league Tokkummaan himna cima!!!!

✍️ግብፅ ለዓመታት ሳውዲ አረቢያን እንደ ፖለቲካዊ ጋሻ በመጠቀም ኢትዮጵያን ከአረቡ ዓለም ለመነጠል የከረመችው ሴራ በአንድ ጀምበር ተናዷል። ትናንት የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ጥረት "ውጤት የሌ...
13/02/2026

✍️ግብፅ ለዓመታት ሳውዲ አረቢያን እንደ ፖለቲካዊ ጋሻ በመጠቀም ኢትዮጵያን ከአረቡ ዓለም ለመነጠል የከረመችው ሴራ በአንድ ጀምበር ተናዷል። ትናንት የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ጥረት "ውጤት የሌለው" እያሉ ሲያላግጡ የነበሩ የካይሮ ልሳኖች፣ ዛሬ ሳውዲ አረቢያ ለኢትዮጵያ የሰጠችውን ታላቅ ክብርና የስትራቴጂክ አጋርነት ሲያዩ ድንጋጤ ውስጥ ወድቀዋል።

🇪🇹ሳውዲ አረቢያ የቀጣናው እውነተኛ ቁልፍ ግብፅ ሳይሆን ኢትዮጵያ መሆኗን በተግባር አሳይታለች። ይህ ለግብፅና ለተባባሪዎቿ "መርዶ" ሲሆን፣ ለኢትዮጵያ ግን የሉዓላዊነትና የቀጣናዊ ፈላጭ ቆራጭነት ማረጋገጫ ድል ነው። ትናንት ሲያሽሟጥጡን የነበሩ፣ ዛሬ የኢትዮጵያንና የሳውዲን አዲስ ጉዞ በቅናትና በውርደት ለመመልከት ተገደዋል‼️

10/02/2026
07/02/2026
📌ታሪክ ራሱን ይደግማል፤ ነገር ግን ለአምባገነኖችና ለደም ነጋዴዎች የታሪክ ድግግሞሽ መርገም ሆኖ ይጸናባቸዋል። ዛሬ በኢትዮጵያ ድንበሮች ላይ የሚታየው ትዕይንት የጉልበት ሳይሆን የውድቀት ዋ...
06/02/2026

📌ታሪክ ራሱን ይደግማል፤ ነገር ግን ለአምባገነኖችና ለደም ነጋዴዎች የታሪክ ድግግሞሽ መርገም ሆኖ ይጸናባቸዋል። ዛሬ በኢትዮጵያ ድንበሮች ላይ የሚታየው ትዕይንት የጉልበት ሳይሆን የውድቀት ዋዜማ፣ የትዕቢት ሳይሆን የባዶነት ማሳያ ነው፤ ለግማሽ ክፍለ ዘመን በጦርነት አዙሪት ውስጥ የኖረውና በንጹሃን ደም የሰከረው የሻዕቢያ ወታደር፣ ዛሬ የዛላምበሳን ቁልቁለትና የኢሮብን ወጣ ገባ ተራሮች ለመውጣት ጉልበት ከድቶታል።

📌የዚህ ድካም ሚስጥር የብረት ክብደት ሳይሆን፣ ያለ ዓላማና ያለ ምክንያት የሌላን ሀገር ድንበር ለመድፈር ከመነሳሳት የመነጨ የሞራል ዝቅጠት፣ ለዘመናት የፈሰሰው የንጹሃን ደም ፣ እና በውሸት ፕሮፓጋንዳ ተገፍቶ የሚገባው ጦርነት መጨረሻው ውርደት መሆኑን ስላረጋገጠ ነው ተስፋ መቁረጥ ስሜት የመነጨ ነው።

📌 ሻዕቢያ በገዛ እጁ የመቃብሩን አፈር እየቆፈረ፣ የገዛ ሞቱን እያፋጠነና የውድቀቱን ድግስ እየደገሰ ይገኛል፤ በክህደት ላይ የቆመው የጥፋት መዋቅርም በኢትዮጵያ ጽናት ፊት ዳግም አመድ ሆኖ መክሰሙ የማይቀየር የታሪክ ፍርድ ነው።

Address

Kofale
Kofele

Telephone

+251910391811

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kofale youth league posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Kofale youth league:

Share

Category