05/12/2023
በሆሳዕና ከተማ ውሃ አገልግሎት ድርጅት ተጨማሪ ውሃ መስፋፋቱ ተገለፀ ።
ህዳር 25/2016 ዓ.ም በሆሳዕና ከተማ ውሃ አገልግሎት ድርጅት ለከተማው ማህበረሰብ የውሃ ጥማት በአጭር ጊዜ ለመቅረፍ በትጋት እየሰራ ይገኛል ከሚሰሩ ስራዎች አንዱ በጃሎ ነራሞ በተለምዶ ዶሮ ዕርባታ ሳይት ፕሮጀክት ስሆን ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአከባቢው ማህበረሰብ የውሃ ስርጭት ሥራ ተጀምሯል ። በውሃ ዕጦት ብዙ ጊዜ ስቸሩ የነበሩ ህብረተሰብ ውሃ ቤት ሆነው ከራሱ ቆጣሪ መቅዳት መጀመሩንም በደስታ ገልጿል ። ይህ ውሃ ለህብረተሰቡ እንዲህ ደረሰ ቀንና ማታ ጊዜ በመስጠት ብዙ ዋጋ እንደተከፈለ የሆሳዕና ከተማ ውሃ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራአስኪያጅ ኢንጂነር ደረጃ ኪዳን ገልጿል ። እንደ ስራአስኪያጁ ገለጻ በሶስት ፕሮጀክት ተከፍለው ከሚሰሩ ፕሮጀክት አንዱ ዶሮ ዕርባታ ሳይት ፕሮጀክት ሲሆን ሥራም በታቀደለት ጊዜ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል የተቀሩት ፕሮጀክቶች ከታቀደለት ጊዜ በጠራ ጊዜው ገደብ እንዲያልቅ በፍጥነት የተሰራ ይገኛል ። ስለሆነም የከተማው የውሃ ደንበኞች ውሃን ከብክነትና ብክለት በመጣበቅ ያለውን ውሃ በንፁህ ውሃ ማጠራቀሚያ ላይ እንዲጠቀሙና ውሃ የተጠቀሙበት ክፊያ በአግባቡ በየወሩ መግቢያ ማለትም ወር ከገባበት ለተከታታይ 25 ቀናት ድረስ ቢል እንዲት ገዙ ገልፀው ቢል ሳይገዛ ሁለት ወር በደረሱት ደንበኞች ላይ በመመሪያና ደንብ መሰረት ቆጣሪ ቆርጦ በመንሳት በቅጣት ያስከፍላል ሁለት ወርና ከዚያ በላይ ስሆን ከደምበኝነት ሙሉ በሙሉ በመሰረዝ ላልተከፈለው ዕዳ ወደ ህግ በማቅረብ ከነዕውዙፍ ዕዳ የሚያስከፍል መሆኑን ተገልጿል ።ምንልበት አንድ አንድ ሰፈሮች የውሃ ዕጥረት ይኖራል ነገር ግን ያለውን ውሃ እየበቀቃን ስለሆነ እስከ ቀሪው ፕሮጄክት መዳረሻ ድረስ በትግስት እንዲት ጠብቁ በታላቅ ትህትና እየጠየቀን ሁሉም ማህበረሰብ የተጀመረውን ፕሮጄክቶች እስኪያልቅ ድረስ የከተማ በለ ሀብት ፣ የከተማችንና የዞናችን እንዲሁም የክልል መንግሥት አስፈለግን ድጋፍና ክትትል እንዲያደርግ ጥሪ ያቀርባል ።
ሆሳዕና ከተማ ውሃ አገልግሎት ድርጅት !!!
ውሃ ህይወት ነው።!!!