Gashaw Asmamaw

Gashaw Asmamaw freedom of speech

25/09/2022
02/07/2022

ለፈገግታ

ኩሩ ህዝብ ኩሩ ጠባቂን ያፈራል! ውድ ኢትዮጵያን በየትኛውም ቦታና ጊዜ የመከላከያ የደንብ ልብስ ለለበሰ አባል ከመቀመጫች ተነስተን ፍጹም ኢትዮጵያ ስርአት የተሞላው ትህትና መስጠት ፣ ማክበር...
15/01/2022

ኩሩ ህዝብ ኩሩ ጠባቂን ያፈራል! ውድ ኢትዮጵያን በየትኛውም ቦታና ጊዜ የመከላከያ የደንብ ልብስ ለለበሰ አባል ከመቀመጫች ተነስተን ፍጹም ኢትዮጵያ ስርአት የተሞላው ትህትና መስጠት ፣ ማክበር አለብን።
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

“ኩሩ ህዝብ ኩሩ ጠባቂን ያፈራል! ውድ ኢትዮጵያን በየትኛውም ቦታና ጊዜ የመከላከያ የደንብ ልብስ ለለበሰ አባል ከመቀመጫች ተነስተን ፍጹም ኢትዮጵያ ስርአት የተሞላው ትህትና መስጠት ፣...

30/12/2021

የአማራን ብሄርተኝነታዊን የህልውና ትግል ከኤሳዊያን፣ከይሁዳዊያን እና ከጲላጦሳዊያን የማጽዳቱ አስፈላጊነት የቅድሚያ ቅድሚያ ተግባር መሆን አለበት!!!

*** ወንድወሰን ተክሉ ***

፠ ብኩርናውን የሸጠ የሕዝብ መሪ መሆን አይቻለውም፦

የአማራን ብሔርተኝነት በመፍጠር የመሰረተ ድንጊያ ያኖሩት ታላቁ ምሁር ፕ/ር አስራት ወልደየስ «የአማራ ሕዝብ ጠላት ሆዳሙ አማራ ነው» ብለውን ነበር። እስቲ ሆዳም አማራን እና ሆዳምነትን ዘርዘር አድርገን በማየት ሆዳም አማራ የአማራ ሕዝብ ጠላት ነው ሲባል ይህንን አይነቱን አማራ ለይቶ ማወቅና መለየት አስፈላጊነቱ ጎልቶ ይቀርባልና ሆዳምነት ምን ማለት ነው ብለን ልንጠይቅ እንችላለን።

ታላቁ ፕ/ር አስራት ወልደየስ የአማራን ሕዝብ ጠላት «ሆዳሙ አማራ ነው» ብለው የገለጹትን እኔ ኤሳዊያን፣ይሁዳዊያን እና ጲላጦሳዊያን በሚል አገላልጽ እነዚህን ስብእናዊ ማንነቶችን ከአማራ ብሄርተኝነትና የህልውና ትግሉ መስመር ካላጸዳን በ1966 የጀመረው የህዝባችን ስቃይ፣ጭቆና፣ጭፍጨፋና ባርነት ለሚቀጥለው ትውልድ የሚሸጋገርበትን ሁኔታ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ Consciously or unconsciously የምንተባበር የመሆናችንን ሀቅ በግልጽ ለማስፈር እወዳለሁ።

ባርነት ስል ምን ለማለት እንደፈለግኩ በመጀመሪያ አጠር አድርጌ ለመግለጽ እፈልጋለሁ። ባርነት የሚለው ቃል ባሪያ ከሚለው ስርወ ቃል የመጣ ሲሆን ባሪያ ማለትም አንድ ሉዓላዊ የሆነ ግለ ተፈጥሮዓዊ ስልጣንና መብቶቹን ተነጥቆ በራሱ ግለ ፍላጎት፣ፍቃድ፣ዓላማና እምነት የማይኖርና እነዚህን ተፈጥሮዓዊ ስልጣንና መብቶቹን ተነጥቆ በሌላ ሰውም ሆነ ኋይል ፍላጎት ፍቃድና ጥቅም ሲል የሚኖር ተገዢ የሆነ ሰው ጥንት በገንዘብ ሲሸጥና ሲገዛ የነበረን ሰው የሚገልጸውን ባሪያን እና ባርነትን የሚገልጽ ነው። ባርነት እንደጥንቱ ነጩ ጥቁሩን የሚሸጥበትና የሚገዛበት ብቻ ሳይሆን ወይንም በሀገራችንም አንድ ሰው ሌላውን ሰው በገንዘብ ሸጦ ወጥም ገዝቶ የግል ሀብትና ንብረቱ አድርጎት እንደሚገልጸው ባሪያ አይነት ትርጉም ያለው ማለት ሳይሆን ማንኛውም ሰው ሆነ ህዝብ ወይም ማህበረሰብ ወደዚህች ምድር ሲመጣ ይዞት የመጣውን ተፈጥሮአዊ የሆነ ሉዓላዊ ስልጣን፣መብት፣ጥቅምና ማንነቱን በነጻነት መጠቀም አቅቶት በሌላ ሰውና ኋይል ተነጥቆ ያለን ተገዢ የሆነ ሰውና ህዝብ በባርነት ውስጥ ያለ ህዝብ ነው በሚል እሳቤ ነው የሕዝባችንን ሁኔታ በባርነት ውስጥ ያለ በሚል ለመግለጽ የፈለግኩት።

ታላቁ የአማራ ሕዝብ ከ1966 ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ በደርግና በኢህአዴግና በብልጽግና በሚባሉ ጸረ አማራ ኋይሎች ስር በባርነት እየማቀቀ ያለ ህዝብ ነው እንጂ በራሱ ጉዳይ እራሱ እየወሰነ እራሱን እየመራ ያለ ሕዝብ ባለመሆኑ በውስጡ በርካታ ኤሳዊያንን፣ይሁዳዊያን እና ጲላጦሳዊያን ተፈጥረው የየራሳቸውን ጨቌኛዊና አስጨቌኛዊ ሚናን ሲጫወቱ ለማየት ችለናል።

አማራ ከ1966 ጀምሮ በጸረ አማራ ኋይል ስር የወደቀ ነው ብንልም ከ1983 ጀምሮ ግን ህዝባችን «የአማራ ሕዝብ ጠላቴ ነች-መቼም ቢሆን እረፍት አንሰጣትም» የሚለውን አቌም የሀገሪቱ ስነ መንግስት መተዳደሪያ ሕገ መንግስት አድርጎ በሚገዛ የለየለት የአማራ ጠላት ኋይል እየተገዛ ያለ ሕዝብ በመሆኑ ይህንን 30ዓመት የአማራ ሕዝብ የባርነት ዘመን ብለን መግለጽ ይቻለናል።

የአማራን የባርነት ዘመን በጉልህ ከሚገልጹ ክስተቶች ውስጥ አማራው ከሁለትሺህ ዘመናት በላይ እውቀቱን፣ባህሉን፣ሀብትና ጉልበቱን እየሰጠ የሀገረ ኢትዮጲያ ስነ መንግስትን በገነባበትና ይህንንም የገነባውን ሀገረ መንግስት ለሺህ ዘመናት ህይወቱን ገብሮ፣ደሙን አፍሥሶና አጥንቱን ከስክሶ

30/12/2021

♦️ ቱሪስት በሚሊዮን ጠርቶ የቱሪዝም ስፍራዎች በገፍ ያሉበትን
የአማራ ክልል ኢንተርኔት መዝጋት ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው?✍️🇪🇹

Address

Tulu Dimtu

Telephone

+251919435757

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gashaw Asmamaw posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gashaw Asmamaw:

Share

Category