Moa Tewahido UK

Moa Tewahido UK Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Moa Tewahido UK, Real Estate, Swansea.

11/07/2023

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዩ ልዩ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ የካህናትና የምእመናን ማኅበራት/ኅብረቶች በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የተሰጠ የጋራ መግለጫ
ሐዋርያዊት እና ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን በየዘመኑ የመጡባትን ፈተናዎች በእግዚአብሔር ቸርነት በቅዱሳን አባቶቻችን ጸሎት ፤ ቁርጠኛ አመራር እና ሰማዕትነት ፤ አንዲሁም በሕዝበ ክርስቲያኑ ጥብአት አልፋ ዛሬ የደረሰቸበት ደረጃ ትገኛለች። በፈተናዎች ውሰጥ ስታልፍ ሁሉን በአገባብ እና በሥርዓት አከናውና ፤ ሥርዓተ ቤተ ክርሰቲያን እና ቀኖናዋን አስጠብቃ ለዘመናት ኖራለች። ከነዚህም አንዱ ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ ሲተላለፍ የመጣው የሥርዓተ ሲመት ቅብብሎሽ እና አፈጻጸም ነው። ኾኖም ግን ካለፉት ጥቂት አሠርት ዓመታት ወዲህ ይህ ቀኖናዊ ትውፊት እየተጣሰ፣ ሥርዓቱም እየፈረሰ መጥቷል። በተለይ መንፈሳዊው ሥልጣን በምድራዊና የጎሳ ፖለቲካ ስሌት እየተሰጠ ሲመጣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሊቃውንትና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላትን በተናጠልና በኅብረት ሲያወያይ ቆይቷል። እኒሁ ሊቃውንትም ለቤተ ክርስቲያኒቱ የበላይ ለኾነው ለቅዱስ ሲኖዶስ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ማሳሰቢያ ሲሰጡበት የቆየ ጉዳይ ነው።
ይኽም ኾኖ መፍትሔ ባለመገኘቱ ምክንያት ከሦስትና አራት ዓመታት ጀምሮ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ምእመናን እና ወጣቶች በተለያየ መልክ በመደራጀት ሲመክሩ ቆይተዋል። በተጨማሪም እነዚሁ የተለያዩ ማኅበራትና ግብረ ኃይሎች የቤተ ክርስቲያኒቱን ወቅታዊ ችግር በመዘርዘርና የመፍትሔ ሐሳብ በመጠቆም ለቅዱስ ሲኖዶስ፣ ለቅዱስ ፓትርያርኩና ለሲኖዶሱ አባላት በተደጋጋሚ እስከ አሁኑ ሰዓት ድረስ በማሳሰብ ላይ ይገኛሉ። ይኹን እንጅ ችግሩ በመሻሻል ፋንታ እየተባባሰና እየከፋ ሂዶ ከላይ እንደተገለጸው ሐዋርያዊው የክህነት ቅብብሎሽ እና ሥርዓተ ሢመት ፈሩን ስቶ በጎሳ መር ፖለቲከኞች የተቃኘ እና ለሕገ ቤተ ክርስቲያን በማይገዙ አባቶች አስፈጻሚነት እየተከወነ ይገኛል። ለዚህም ዋቢ የሚኾነው በፈጸሙት ሕገ ወጥ ሢመትና ያንንም ተከትሎ ለብዙ ምእመናን ሕልፈተ ሕይወት ምክንያት በመኾናቸው ቅዱስ ሲኖዶሱ በጥር ፲፰ ቀን ፳፻፲፭ ዓ. ም. ያወገዛቸውን አባቶች መልሶ ከቀኖና ውጭ በየመንበራቸው ማስቀመጡና ይባስ ብሎም ከእኒሁ ተመላሽ አባቶች ለኤጲስ ቆጶሳት መራጭ ኮሚቴ ሰብሳቢ ማድረጉ ነው። ይህ አካሄድ ለማንኛውም ኦርቶዶክሳዊ በእጅጉ ልብ የሚሰብርና በቀጣይነትም የቤተከርሰቲያን አንድነትን የሚያናጋ ነው። ይኽ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሂደት በዚሁ ሁኔታ ከቀጠለ ቤተ ክርስቲያኒቱን በግልጽ ወደማትወጣበት አዘቀት ውስጥ የሚያስገባት መኾኑ እሙን ነው። በመኾኑም እነዚህ ከክርሰትና መርሆዎችና ከቤተ ክርስቲያናችንም ቀኖና ባፈነገጠ መልኩ ከዘመኑ የጎሳ ፖለቲካዊ እሳቤ ጋር የተጣበቁ ሂደቶች እና ድብቅ
ውሳኔዎች የቤተ ክርስቲያንን ህልውና የሚገዳደሩ መሆናቸውን ቅዱስ ሲኖዶስ ልብ ሊለው ይገባል። ምክንያቱም እንዲህ ያሉ አካሄዶች ለቤተ ክርስቲያናችን ታላቅ የታሪክ ስብራቶች ከመኾናችውም ባሻገር ውሉደ ከህነትንና ሊቃውነተ ቤተክርስቲያንን እንዲሁም ህዝበ ክርስቲያኑን በእጅጉ እያስጨነቁ ያሉ በመኾናቸው ነው። ከዚህም አልፎ ሕግ አለበት በሚባል ሀገር ውስጥ ቤተ ክርስቲያናችን ሕጓ ሲጣስና ያለ ቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ ሕገ ወጦች በማን አለብኝነት “ኤጲስ ቆጶሳትን” ሾምን ባሉበት ሰዓት ቅዱስ ሲኖዶስ ባወጣቸው
ጥሪዎቸ ኹሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች ከልሂቅ እስከ ደቂቅ ጥሪውን ተቀብለን በአነድነት ተገባራዊ ስናደርግና በዚህም ጥፋተኞቹ እንዲመለሱና የቤተ ክርስቲያናችን ቀኖናም እንዲከበር ማስቻላችን የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው። በአንጻሩ ቅዱስ ሲኖዶስ አሁን እየሔደበት ያለው መንገድ ያንን ሕዝበ ክርስቲያኑ በደም መሥዋዕትነት፣ በዕንባና በጸሎት ያስከበረውን ቀኖና በመጣስ ላይ ይገኛል። ከዚህም አልፎ የሊቃውንቱን፣ የማኅበረ ካህናትና ምእመናንን ተደጋጋሚ ጩኸት እንደ ኢምንት ቆጥሮ በማን አለብኝነት ቤተ ክርስቲያናችንን ወደ ጥፋት ጎዳና እየመራት መሆኑ በጣም አስደንጋጭና አሳዛኝ ኩነት ነው። በመኾኑም ቤተ ክርስቲያናችን ከላይ ከተጠቀሱት ምስቅልቅል ችግሮች ትድን ዘንድ አሁንም ጊዜው ስላልረፈደ ቅዱስ ሲኖዶስ የሚከተሉትን እርምጃዎች ይወስድ ዘንድ ለመጨረሻ ጊዜ እናሳስባለን፦
፩. ቤተ ክርስቲያንን ከከፋ ክፍፍል መታደግ ይቻል ዘንድ በአሁኑ ሰዓት ይፈጸማል የተባለውና ቀኖናን ከመጣስ ባሻገር በውስጡ ፖለቲካዊ ከፋፋይ ሤራ ያጠላበት በመኾኑ ብዙ ሊቃውንትንና ሕዝበ ክርስቲያንን እያስጨነቀ የሚገኘው ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትን ቅዱስ ሲኖዶስ እንዲሠርዝ እንጠይቃለን፤
፪. በአጠቃላይ እየታየ ያለውን የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀኖናዊና አስተዳደራዊ ችግር ከሥር መሠረቱ ማስተካከል ይቻል ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶሱ ባስቸኳይ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሊቃውንት፣ ካህናትና ምእመናንን ያሳተፈ ዓለም አቀፍ ጉባኤ እንዲያዘጋጅና በውጤቱም ዘመኑን የዋጀ አስተዳደራዊ መዋቅር በመዘርጋትና ቀኖናውንም በማስተካከል የቤተ ክርስቲያንን ህልውና እና ልዕልና እንዲያስጠብቅ እንጠይቃለን።
፫. ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ማድረግ የማትይችል ከሆነ፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን ይከበር ዘንድ ቁርጥ ኅሊና ያላቸውን ሊቃነ ጳጳሳት መሪ በማድረግ የሕገ ወጥ ኤጲስቆጶሳት ሹመትን በጥብዓት የምንታገልና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የማስከበር ሃይማኖታዊ ግዴታችንን ለመወጣት የምንገደድ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን።
፬. ለኤጲስ ቆጶስነት በእጩነት ለተመረጣችሁ መነኮሳት፦ ምንም እንኳ ሹመቱ ሊገባችሁ የምትችሉ ብትኖሩም ይህ ሹመት ያለ ጊዜውና ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ የመጣና ከመንፈሳዊነቱ ይልቅ ፖለቲካዊ ተልዕኮ ያለበት መሆኑን ተገንዝባችሁ እጩነቱን ባለመቀበል ራሳችሁን እንድታገልሉና ቤተ ክርስቲያናችሁን ከከፋ አደጋ እንድትታደጉ እናሳስባለን።
ሐምሌ ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ. ም.
፩. ፍኖተ ጽድቅ ወሕይወት፣ ጉባኤ ማኅበራ ለቤተ ክርስቲያን፣ ዓለም አቀፍ ኅብረት
፪. ማኅበረ ካህናት ዘሰሜን አሜሪካ
፫. የዩኬና አየርላንድ ማኅበረ ካህናት
፬. ሞዐ ተዋሕዶ ግብረ ኃይል
፭. የነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር በአውሮፓ

Address

Swansea
SA14JP

Telephone

+447576108316

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Moa Tewahido UK posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Moa Tewahido UK:

Share

Category