selam

selam Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from selam, Real Estate, dubai, Duhat.

16/07/2026

ጋር Instagram – ከእነሱ ዋና አድናቂዎች እንደ አንዱ ሆኜ አሁን እውቅና አግኝቻለሁ!የሰነድ አለመኖር የካሳ መብትን ያሳጣልን?
***********
​ለመሆኑ አንድ ግለሰብ ለአሥርተ ዓመታት የቆየ ይዞታ እያለው፣ ይዞታውን የሚያረጋግጥ "የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ወይም ደብተር" ስለሌለው ብቻ ያለ ካሳ ከመሬቱ እንዲፈናቀል ሕጉ ይፈቅዳል?

​የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 198400 (ሐምሌ 27 ቀን 2013 ዓ.ም) በሰጠው ውሳኔ ለዚህ ጥያቄ ግልጽ ምላሽ ሰጥቷል።

​ የክርክሩ መነሻ

​አመልካች በጅማ ከተማ ውስጥ ለረጅም ዘመን የቆየ ይዞታ ያላቸው ሲሆን፣ የከተማው አስተዳደር "ይዞታው ለሕዝብ ጥቅም ይፈለጋል" በሚል ለልማት ሲነሳ አመልካች "የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ (ካርታ) የላችሁም" በሚል ካሳ ሳይከፈል እንዲነሱ መወሰኑ ክርክሩን አስነስቶታል።

​ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ

​መደበኛ ፍርድ ቤቶች "አመልካች በቅድሚያ የይዞታ ማረጋገጫ ማውጣት ነበረባቸው" በሚል የሰጡትን ውሳኔ የሰበር ሰሚ ችሎቱ በመሻር የሚከተሉትን መሠረታዊ የሕግ ነጥቦች አስፍሯል፦
​የሕገ-መንግሥታዊ ጥበቃ፦ በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 40(1) እና (7) መሠረት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም በገንዘቡ በሠራው ንብረት ላይ ሙሉ መብት አለው። መንግሥት ለሕዝብ ጥቅም ሲል ንብረቱን በሚወስድበት ጊዜም ተመጣጣኝ ካሳ በቅድሚያ የመክፈል ግዴታ አለበት።

​የሰነድ አለመኖር እና የይዞታ መብት፦ አንድ ግለሰብ ይዞታው ላይ ለረጅም ዘመን መቆየቱ እየታወቀ፣ አስተዳደራዊ በሆኑ ምክንያቶች ወይም በወቅቱ የነበሩ አሠራሮች ባለመኖራቸው ምክንያት የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ ባይኖረውም፣ ይዞታው ለሕዝብ ጥቅም ሲፈለግ "ሰነድ የለህም" በሚል ብቻ ያለምንም ካሳ እንዲነሳ ማድረግ የሕግ መሠረት የለውም።

​የአስተዳደሩ ግዴታ፦ ይዞታው ለሕዝብ ጥቅም ሲፈለግ፣ አስተዳደሩ በቅድሚያ ይዞታው የአመልካች መሆኑንና ለምን ያህል ጊዜ እንደቆዩ አጣርቶ ተገቢውን ካሳ ሊከፍል ይገባል እንጂ፣ ካሳ ላለመክፈል የሰነድ አለመኖርን እንደ መከላከያ ሊጠቀምበት አይችልም።

​ይህ ውሳኔ በተለይ በከተማም ሆነ በገጠር በይዞታቸው ላይ ለረጅም ዘመን የቆዩ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ (ካርታ) ያልወጣላቸው ዜጎች፣ ለልማት ሲነሱ የመካስ መብታቸውን የሚያስከብር ነው።
#መላኩ ፍቃዱ

የሰነድ አለመኖር የካሳ መብትን ያሳጣልን?***********​ለመሆኑ አንድ ግለሰብ ለአሥርተ ዓመታት የቆየ ይዞታ እያለው፣ ይዞታውን የሚያረጋግጥ "የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ወይም ደብተር" ...
16/07/2026

የሰነድ አለመኖር የካሳ መብትን ያሳጣልን?
***********
​ለመሆኑ አንድ ግለሰብ ለአሥርተ ዓመታት የቆየ ይዞታ እያለው፣ ይዞታውን የሚያረጋግጥ "የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ወይም ደብተር" ስለሌለው ብቻ ያለ ካሳ ከመሬቱ እንዲፈናቀል ሕጉ ይፈቅዳል?

​የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 198400 (ሐምሌ 27 ቀን 2013 ዓ.ም) በሰጠው ውሳኔ ለዚህ ጥያቄ ግልጽ ምላሽ ሰጥቷል።

​ የክርክሩ መነሻ

​አመልካች በጅማ ከተማ ውስጥ ለረጅም ዘመን የቆየ ይዞታ ያላቸው ሲሆን፣ የከተማው አስተዳደር "ይዞታው ለሕዝብ ጥቅም ይፈለጋል" በሚል ለልማት ሲነሳ አመልካች "የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ (ካርታ) የላችሁም" በሚል ካሳ ሳይከፈል እንዲነሱ መወሰኑ ክርክሩን አስነስቶታል።

​ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ

​መደበኛ ፍርድ ቤቶች "አመልካች በቅድሚያ የይዞታ ማረጋገጫ ማውጣት ነበረባቸው" በሚል የሰጡትን ውሳኔ የሰበር ሰሚ ችሎቱ በመሻር የሚከተሉትን መሠረታዊ የሕግ ነጥቦች አስፍሯል፦
​የሕገ-መንግሥታዊ ጥበቃ፦ በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 40(1) እና (7) መሠረት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በጉልበቱ ወይም በገንዘቡ በሠራው ንብረት ላይ ሙሉ መብት አለው። መንግሥት ለሕዝብ ጥቅም ሲል ንብረቱን በሚወስድበት ጊዜም ተመጣጣኝ ካሳ በቅድሚያ የመክፈል ግዴታ አለበት።

​የሰነድ አለመኖር እና የይዞታ መብት፦ አንድ ግለሰብ ይዞታው ላይ ለረጅም ዘመን መቆየቱ እየታወቀ፣ አስተዳደራዊ በሆኑ ምክንያቶች ወይም በወቅቱ የነበሩ አሠራሮች ባለመኖራቸው ምክንያት የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ ባይኖረውም፣ ይዞታው ለሕዝብ ጥቅም ሲፈለግ "ሰነድ የለህም" በሚል ብቻ ያለምንም ካሳ እንዲነሳ ማድረግ የሕግ መሠረት የለውም።

​የአስተዳደሩ ግዴታ፦ ይዞታው ለሕዝብ ጥቅም ሲፈለግ፣ አስተዳደሩ በቅድሚያ ይዞታው የአመልካች መሆኑንና ለምን ያህል ጊዜ እንደቆዩ አጣርቶ ተገቢውን ካሳ ሊከፍል ይገባል እንጂ፣ ካሳ ላለመክፈል የሰነድ አለመኖርን እንደ መከላከያ ሊጠቀምበት አይችልም።

​ይህ ውሳኔ በተለይ በከተማም ሆነ በገጠር በይዞታቸው ላይ ለረጅም ዘመን የቆዩ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ (ካርታ) ያልወጣላቸው ዜጎች፣ ለልማት ሲነሱ የመካስ መብታቸውን የሚያስከብር ነው።
#መላኩ ፍቃዱ

04/07/2026
የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይደረጋልአዲስ አበባ (ሰኔ 22/2018 ዓ.ም)፦ የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ...
29/06/2026

የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይደረጋል

አዲስ አበባ (ሰኔ 22/2018 ዓ.ም)፦ የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት በኋላ ይፋ እንደሚደረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

ውጤቱ ይፋ የሚደረገው የቢሮው የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ነጥቡ ላይ ውይይት ካደረጉ በኋላ ነው።
ይህ የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለ85,737 ተማሪዎች መሰጠቱ ይታወሳል።

የዘንድሮው ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ውጤታቸውን በጊዜ አውቀው ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል መሆኑን ቢሮው ገልጿል።

Via የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ

ጉርሻ Page

🌴🌴🌴

ሁለንተናዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶች ያለአንዳች መዘናጋት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ፦ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )ሆሳዕና ፣ሰኔ 22 ፣2018፦የማዕከላዊ ኢትዮጵ...
29/06/2026

ሁለንተናዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶች ያለአንዳች መዘናጋት ተጠናክረው ይቀጥላሉ ፦ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር )

ሆሳዕና ፣ሰኔ 22 ፣2018፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፣ በልዩ ትኩረት እየተመሩ የሚገኙ ተግባራትን ወቅታዊ የአፈጻጸም ደረጃ በበይነ መረብ አማካይነት ዛሬ ገምግመዋል፤ ቀጣይ አቅጣጫዎችም ተመላክተዋል።

የአፈጻጸም ግምገማው በፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ፣ በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከላት ዝግጅት ፣በኢትዮ ኮደርስ ስልጠና፣ በገቢ አሰባሰብ ፣በከተማና በገጠር ኮሪደር ልማት ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች አፈጻጸም፣ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እና ኑሮ ውድነትትን ማረጋጋት በተመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ መሆኑ ተመልክቷል።

የተግባራቱን ወቅታዊ አፈጻጸም ደረጃ የተመለከተ ሪፖርት በሚመለከታቸው ቢሮዎች ኃላፊዎች በኩል ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፣ በመድረኩ ማጠቃለያ እንደገለፁት ፤ ሁለንተናዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሻሻል የተጀመሩ ጥረቶች ያለአንዳች መዘናጋት ተጠናክረው ይቀጥላሉ።

እየተጠናቀቀ በሚገኘው በጀት ዓመት ቀሪ ጊዜያትም ይሁን በመጪው አዲሱ በጀት ዓመት ፣ በሁሉም መስኮች የህዝቦችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ የየደረጃው አመራር በትጋት መንቀሳቀስ የሚጠበቅበት መሆኑን ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) አፅንኦት ሰጥተው አሳስበዋል ።

በሁለተኛው ዙር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንቅስቃሴ የወራቤ፣ የወልቂጤ፣ የሆሳዕና ፣ የሀላባ ቁሊቶ እና የዱራሜ ከተሞች ማዕከላት ተጠናቅቀው ለአገልግሎት ክፍት መሆናቸው በመደረኩ የተጠቀሰ ሲሆን ፣የቡታጅራ ከተማ ማዕከልም ከጥቂት ቀናት በኋላ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ተገልጿል።

ተጠናቅቀው ለአገልግሎት ክፍት የሆኑ ማዕከላት ወደተሟላ መንግስታዊ አገልግሎት መስጠት ስለመግባታቸዉ በየመቅሩ የቅርብ ክትትል እንዲደረግ አቅጣጫ ተቀምጧል ።
ከፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ አንፃር እስከ ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ ባለው ጊዜ በክልሉ ከ3 ሚሊየን 1መቶ ሺህ በላይ ያህል ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ መውሰዳቸው በመድረኩ ተገልጿል ።

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናውም ተጠናክሮ መቀጠሉ በውይይቱ የተዳሰሰ ሲሆን፣ ሰልጣኞች ስልጠናውን በአግባቡ አጠናቅቀው ሰርተፍኬት የሚወስዱበት ሁኔታ በትኩረት እንዲመራ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ከገቢ አሰባሰብ አንፃር እስከ ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ 24 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡ የተጠቀሰ ሲሆን ፣ይህም በበጀት ዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው 27 ቢሊየን ብር ዕቅድ አንፃር አፈጻጸሙ 91 ነጥብ 5 በመቶ መደረሱን ያመለክታል ተብሏል ።

በከተማ እና በገጠር ኮሪደር ልማት ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች አፈጻጸም፣ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እና ኑሮ ውድነትትን ማረጋጋትን በተመለከቱ ጉዳዮች ወቅታዊ አፈፃፀም ሁኔታ ዙሪያ ዝርዝር ውይይት ተደርጓል ፤ ቀጣይ አቅጣጫዎችም ተቀምጠዋል።

በመድረኩ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር ) ጨምሮ የክልሉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣ የክልሉ ካብኔ አባላት፣ የዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች ዋና አስተዳዳሪዎች እና አስተባባሪ ኮሚቴዎች እንዲሁም ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።

‎ከዲላ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የተሰጠ መግለጫ‎‎ #ዲላ ስኔ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ዲላ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግኑኝነት።‎‎በዲላ ከተማ አስተዳደር  አንድት ህፃን ሴ...
29/06/2026

‎ከዲላ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የተሰጠ መግለጫ

‎ #ዲላ ስኔ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ዲላ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግኑኝነት።

‎በዲላ ከተማ አስተዳደር አንድት ህፃን ሴት ልጅ ዶሮ ስርቃለች በማለት በታጣቅዋች አማካይነት የስብዓዊ መብት ጥሰት ስፈጸም የምያሳይ ፎቶ ተመልክተና

‎ጉዳዩ የተፈፀመው ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ/ም በዲላ ከተማ ሚችለ ክ/ከተማ ሀሰደላ ቀበሌ አስተዳደር ክልል ውስጥ ስሆን ህፃን ሴት ልጅ ዶሮ ስርቀሻል በማለት በታጣቂዎች አማካይት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ተፈጸሞባታል ።

‎የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሰፈፀም ለዲላ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የተሰጠ ጥቆማ ባይኖረም ከሁለት ወር በኃላ ሰኔ 20 ቀን 2018 ዓ/ም ጉዳዩ በማህበራዊ ሚድያ ወጥቶ ተመለከተናል በድርግቱ የተሳተፋትን አምስት ተጠርጣሪዎች ይዘን በህግ ቁጥጥር ስር አውለናል በወንጀል ምርመራ የማጣራት ስራ ይሰራል ።

‎የተፈፀመውን የስብዓዊ መብት ጥሰት በመቃወም ጥቆማ የሰጣችሁን አካል እናመሰግናለን ቀጣይ የደረስንበትን ለህዝብ እናሳውቃለን ።

‎@ዲላ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግኑኝነት


የሲጋራ ቁራጭ 2 ሺህ ብር ሊያስቀጣ ነው‼በአዲስ አበባ ከተማ የሲጋራ ቁራጭ በመንገድ፣ በአደባባይ ወይም በማንኛውም የሕዝብ መገልገያ ቦታ ላይ የሚጥል ግለሰብ በ2 ሺህ ብር እንደሚቀጣ የአዲስ...
29/06/2026

የሲጋራ ቁራጭ 2 ሺህ ብር ሊያስቀጣ ነው‼

በአዲስ አበባ ከተማ የሲጋራ ቁራጭ በመንገድ፣ በአደባባይ ወይም በማንኛውም የሕዝብ መገልገያ ቦታ ላይ የሚጥል ግለሰብ በ2 ሺህ ብር እንደሚቀጣ የአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አስታወቀ።

ቅጣቱ የሚተገበረው የትምባሆ ምርቶችን አጠቃቀም ለመቆጣጠር በወጣው የከተማ አስተዳደሩ ደንብ ቁጥር 167/2016 መሠረት መሆኑን የባለሥልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ሙሉእመቤት ታደሰ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በከተማዋ 79 በመቶ የሚሆኑት የሕዝብ መገልገያ ተቋማት ከጭስ ነፃ መሆናቸውንና የአጫሾች መጠን ከ5.3 በመቶ ወደ 4.6 በመቶ መቀነሱን ባለሥልጣኑ አመልክቷል ሲል ብስራት ሬዲዮ ዘግቧል።

27/06/2026

በአፖሎ የዶላር አካውንት ያስቀምጡ፤ ከባሕር ማዶ እንዳሻዎ ይገበያዩ።
ዛሬ ይመዝገቡ እና በደቂቃዎች ውስጥ ይጀምሩ 👉 https://onelink.to/apollo@

⚖️ የማስረጃ ምዘና፣ አሰማም እና የክርክር ሥርዓት ቁልፍ መርሆዎች 📜1. 🔍 የምስክርነት ቃልን እና የሰነድ ማስረጃን ስለመመዘን➡️ ሁሉንም ዓይነት ማስረጃ የመመርመር ግዴታ: ፍርድ ቤቶች ለ...
27/06/2026

⚖️ የማስረጃ ምዘና፣ አሰማም እና የክርክር ሥርዓት ቁልፍ መርሆዎች 📜

1. 🔍 የምስክርነት ቃልን እና የሰነድ ማስረጃን ስለመመዘን

➡️ ሁሉንም ዓይነት ማስረጃ የመመርመር ግዴታ: ፍርድ ቤቶች ለክርክሩ ፍትሐዊነትና ትክክለኛ ውሳኔ መስጠት ተገቢ ነው ብለው ያመኑትን ማናቸውንም ዓይነት ማስረጃ አስቀርበው የመመርመር ግዴታ አለባቸው (ሰ/መ/ቁ. 207967)።

➡️ የማስረጃ ምዘና መርህን ስለመጣስ: ፍርድ ቤቶች የቀረቡላቸውን ማስረጃዎች በሙሉ (የሰው ምስክርም ሆነ የሰነድ) መርምረውና መዝነው ፍሬ ነገርን የማጣራት ኃላፊነት አለባቸው (ሰ/መ/ቁ. 208495)። በተለይም፣ የቀረበን የሰነድ ማስረጃ ከግምት ውስጥ ሳያስገቡ ወይም ሳይመረምሩ በሰው ምስክሮች ቃል ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚሰጥ ውሳኔ የማስረጃ ምዘና መርህን የሚጥስና መሰረታዊ የህግ ስህተት ያለበት ነው (ሰ/መ/ቁ. 208495)።

➡️ የጽሑፍ ውል ይዘት ቅድሚያ: በሕግ አግባብ የተከናወነ የጽሑፍ ውል ይዘት ሙሉ እምነት የሚጣልበት በቂ ማስረጃ ስለሆነ፣ ውሉን በምስክር ቃል ማስተባበል አይቻልም (ሰ/መ/ቁ. 235005)። በመሆኑም ፍርድ ቤት የጽሑፍ ውልን ሳይመዘን በሰው ምስክሮች ቃል ላይ ብቻ ተመርኩዞ መወሰን መሰረታዊ የማስረጃ ምዘና ስህተት ነው (ሰ/መ/ቁ. 235005)።

➡️ የተረጋገጠ ሰነድ አስገዳጅነት: በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ (DOAR) ስልጣን ባለው አካል የተረጋገጠ እና የተመዘገበ ሰነድ ሙሉ እምነት የሚጣልበት በቂ ማስረጃ ነው፤ ስለዚህ የውክልና ሰነድ በሰው ምስክር ሊስተባበል እንደማይችል መገንዘብ ይገባል (ሰ/መ/ቁ. 201608)።

➡️ የቀድሞ ውሳኔን እንደ ብቸኛ ማስረጃ መውሰድ: ቀደም ሲል በቀረበ ክስ ላይ የተሰጠ ውሳኔን እንደ ብቸኛ በቂ ማስረጃ በመቁጠር የሌላኛውን ወገን ማስረጃ ሳይመዝኑ ፍርድ መስጠት የማስረጃ ምዘና መርህን የሚጥስ መሰረታዊ የሙግት አመራር ስህተት ነው (ሰ/መ/ቁ. 206676)።

➡️ ማስረጃን አለመቀበልና ምክንያት: የፍርድ ቤት ውሳኔ በግራ ቀኙ ከቀረቡት ማስረጃዎች አጠቃላይ ይዘት ጋር በማገናዘብ መሆን ሲገባው፣ ፍርድ ቤቱ ለውሳኔ የሚያስፈልጉትን ማስረጃዎች ብቻ በመውሰድ ሌላውን ያልተቀበለበትን ምክንያት ሳይገልጽ ውሳኔ መስጠቱ የማስረጃ ምዘና መርህን ያልተከተለ ነው (ሰ/መ/ቁ. 207967)።

2. 🗣 የምስክር ቃል አሰማም እና የክርክር ሥርዓት (Procedural Requirements)

➡️ የአንዱን ወገን ምስክር ቃል ሳይሰሙ ማለፍ: አንድ የፍሬ ነገር ጭብጥ በሰው ምስክሮች እንዲጣራ ትዕዛዝ ከተሰጠ በኋላ፣ የአንድ ወገን ምስክሮች ሳይሰሙ ውሳኔ መስጠት የፍርድ አመራር ሥርዓት መርህን የሚጥስና መሰረታዊ የህግ ስህተት ነው (ሰ/መ/ቁ. 205709, 223270)።

➡️ በዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ላይ ያለመወሰን: በወንጀል ክስ፣ ወንጀሉ መፈጸሙን የማስረዳት ኃላፊነት የዐቃቤ ሕግ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ የዐቃቤ ሕግን ማስረጃ ሳይሰማ፣ በተከሳሽ በቀረበው ማስረጃ ላይ ብቻ ተመስርቶ ዐቃቤ ሕግ ክሱን አላስረዳም በሚል በነፃ መልቀቅ መሰረታዊ የክርክር አመራር መርህን የተከተለ አይደለም (ሰ/መ/ቁ. 235007)።

➡️ የተጨማሪ ማስረጃ አግባብነት: ፍርድ ቤት ለትክክለኛ ፍርድ አሰጣጥ ተጨማሪ ማስረጃ እንዲቀርብ ካዘዘ፣ በቀረበው ማስረጃ (ለምሳሌ የባለሙያ ማብራሪያ) ላይ የግራ ቀኙን አስተያየት በመቀበልና በመስማት ተገቢውን ውሳኔ መስጠት ይገባዋል፤ ሳይሰማ መወሰን የመሰማት መብትን ይጋፋል (ሰ/መ/ቁ. 206044)።

ምንጭ:- Abrham Yohanes

በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ሀገሪቱን ጥለው እየሸሹ ነው!እንደ አልጀዚራ (Al Jazeera) የዜና ዘገባ ከሆነ በደቡብ አፍሪካ በተቀሰቀሰው ከፍተኛ የውጭ ዜጎች ጥላቻ ...
27/06/2026

በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ሀገሪቱን ጥለው እየሸሹ ነው!

እንደ አልጀዚራ (Al Jazeera) የዜና ዘገባ ከሆነ በደቡብ አፍሪካ በተቀሰቀሰው ከፍተኛ የውጭ ዜጎች ጥላቻ (Xenophobia) እና ጥቃት ምክንያት፣ እንዲሁም June 30 ሊደረግ ከታቀደው መጠነ-ሰፊ ፀረ-ስደተኞች ሰልፍ አስቀድሞ በሺዎች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን ስደተኞች ሀገሪቱን በከፍተኛ ስጋት እየለቀቁ ይገኛሉ።

እንደ ማላዊ፣ ዚምባብዌ፣ ናይጄሪያ፣ ጋና እና ሞዛምቢክ ያሉ የአፍሪካ ሀገራት መንግስታት ዜጎቻቸውን በፈቃደኝነት ወደ ሀገራቸው ለመመለስ (Repatriation) የአውቶቡስ እና የሎጂስቲክስ ዝግጅቶችን እያደረጉ ሲሆን፣ በርካታ ስደተኞችም ጥበቃ ፍለጋ በየሀገራቱ ቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች ደጅ ላይ ተሰባስበው ይገኛሉ።

ይህ የጊዜ ገደብ መጀመሪያ ላይ የደቡብ አፍሪካን መንግስት አርማ ተጠቅሞ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት በተሰራጨ የሀሰት (AI-generated) ፖስተር የተነሳ የመጣ ቢሆንም፣ "ማርች ኤንድ ማርች" (March and March) የተባሉ የፀረ-ስደተኛ አደረጃጀቶች እና ቡድኖች ግን ህገ-ወጥ ስደተኞች በሙሉ እስከ June 30 ድረስ ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ በማስገደድ የራሳቸውን መጠነ-ሰፊ ዘመቻ ከፍተዋል።

ምንም እንኳን የተሰጠው የጊዜ ገደብ ህጋዊ ባይሆንም፣ በተለያዩ ከተሞች (ለምሳሌ በሞሰል ቤይ) በስደተኞች መኖሪያ ላይ ጥቃት ተሰንዝሯል፣ ቤቶች ተቃጥለዋል፣ ንብረቶች ተዘርፈዋል እንዲሁም የሰው ህይወት ጠፍቷል።

ጋና በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎቿን በልዩ የአየር በረራ የመለሰች ሲሆን፣ ማላዊ ከ5,000 በላይ ሰዎችን በባስ ለማጓጓዝ እየሰራች ነው።

ናይጄሪያ እና ሞዛምቢክም በተመሳሳይ ሁኔታ ዜጎቻቸውን የማስወጣት ስራ ላይ ናቸው።

የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ (SAPS) June 30 ሊደረግ የታቀደውን ሰልፍ ተከትሎ ሁከት እንዳይፈጠር 600 ሚሊዮን ራንድ (R600-million) የሚጠጋ ከፍተኛ በጀት መድቦ ፖሊሶችን በሙሉ አቅም እያሰማራ ይገኛል።

ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ በበኩላቸው በህገ-ወጥ ስደተኞች ላይ ጥብቅ የስራ ቦታ ፍተሻ እና ቁጥጥር እንደሚደረግ ቢገልጹም፣ በስደተኞች ላይ የሚደረገውን ህገ-ወጥ ጥቃት እና ማስፈራሪያ ግን ኮንነዋል።

በሀገሪቱ ያለው ከፍተኛ የስራ አጥነት፣ የወንጀል መስፋፋት እና የኢኮኖሚ ቀውስ፣ አንዳንድ ፖለቲከኞች እና የፀረ-ስደተኛ ቡድኖች ስደተኞችን ለችግሩ ዋነኛ ተጠያቂ (Scapegoats) እንዲያደርጓቸው ምክንያት ሆኗል።



Via Aljazeera

በደቡብ አፍሪካ በስደት ላይ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን እህትና ወንድሞቻችን፤ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ ከወዲሁ እናሳስባለን።

ጉርሻ Page

🌴🌴🌴

Address

Dubai
Duhat
NO

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when selam posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category