Gadaa Online

Gadaa Online Ye Ethiopia Kefita be 2015 Gadaa is the only law of Oromo for many 1000 years!

07/27/2023
የማህበረሰብ አንቂነትና ጋዜጠኝነትን በሽፋን ታጥቀው ዛሬም የህዝቦችን አብሮ የመኖርና የመከባብር እሴትን ለመናድ እና ሰላምን ለማደፍረስ  የሚጥሩ አካላት ዛሬም አላረፉም።የአማራ ህዝባዊ ግንባ...
07/27/2023

የማህበረሰብ አንቂነትና ጋዜጠኝነትን በሽፋን ታጥቀው ዛሬም የህዝቦችን አብሮ የመኖርና የመከባብር እሴትን ለመናድ እና ሰላምን ለማደፍረስ የሚጥሩ አካላት ዛሬም አላረፉም።
የአማራ ህዝባዊ ግንባር በሚል የሚጠራውን ፀረ-ሰላም ሀይል ዛሬም የማህበረሰብ አንቂ ነን የሚሉና በጋዜጠኝነት ሽፋን የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን ተጠቅመው የግል ጥቅማቸውን ለማካበት ሲሯሯጡ ይስተዋላል።
ይኸው የፀረ-ሰላምን አሁን ደግሞ በፋይናንስ ለማጠናከር በሚል እንደለመዱት የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ገንዘብ ለመዝረፍ ፕሮግራም ማዘጋጀታቸው እየተነገረ ነው።
የአማራ ህዝባዊ ግንባር በሚል የሚጠራውን ፀረ-ሰላም ሀይል የሚዲያ ክንፍ አስተባባሪ የሆነው ወግደረስ ጤናው በዚው የገንዘብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ተሳታፊ እንደሚሆን ነው እየተገለጸ ያለው።
ለመብት የታገሉ በመምሰል ትላንት የማህበረሰብ አንቂዎች ነን የሚሉ እና የጋዜጠኝነትን ሽፋን ተላብሰው ለህዝብ የተቆረቆሩ በመምሰል ነገር ግን ኪሳቸውን ለመሙላት ከሚሯሯጡ ግለሰቦች መካከል አንዱ ወግደረስ ጤናው ነው።
ከዚህ በፊት በማህበራዊ ሚዲያም ሆነ በተለያዩ መድረኮች አብሮ በኖረ ህዝቦች መካከል ጥላቻን እና ሃሰትን በመንዛት በስንቶች መስዋትነትና ተጋድሎ የተገኘን ሰላም ለማደፍረስ ሲሯሯጥ ተስተውሏል።
በተለይ የአማራ ህዝብ ከጎረቤት ህዝብ ጋር ተሳስቦና ተከባብሮ መኖር እንዳይችል ሲጥር የነበረ ይግ ግለሰብ ዛሬም እንደተለመደው በትግል ስም በውጭ ለሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት የተሳሳተና ሃሰተኛ መረጃ በመስጠት ሀንዘብ እንዲያዋጡ በማድረግ ኪሳቸውን የማደለብ ስራን በመስራት ላይ ናቸው ።
በየትኛውም ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውለደ ኢትዮጰያውያን ህሊናቸውን ሸጠው ከርሳቸው ለመሙላት የሚሯሯጡት እነ ወግደረስ ጤናው መሰሎቹን በቃ ሊላቸው ይገባል።

የፓርቲወቹ የጋራ መግለጫ እና የሳቱት ነጥብእናት ፓርቲ ከሌሎች አራት አጋር የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን ዛሬ ባወጡት መግለጫ ሃገሪቷ ላይ ያለውን ወቅታዊ ችግር ለመፍታት መንግስት ከ...
07/13/2023

የፓርቲወቹ የጋራ መግለጫ እና የሳቱት ነጥብ
እናት ፓርቲ ከሌሎች አራት አጋር የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን ዛሬ ባወጡት መግለጫ ሃገሪቷ ላይ ያለውን ወቅታዊ ችግር ለመፍታት መንግስት ከታጣቂ ሃይሎች ማለትም ከፋኖ እና ሸኔ ጋር የሲቪክ ማህበራት እና ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲወች ባሉበት የጋራ ንግግር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። ፓርቲወቹ ይህን ይበሉ እንጂ መንግስት ችግሮችን በንግግር ለመፍታት ያለውን ቁርጠኝነት በተደጋጋሚ ያሳየ ሲሆን ፤ እነዚህ ኢመደበኛ ሃይሎች ግን ለንግግር ፈጽሞ ቦታ እንደሌላቸው በታንዛንያ የተካሄደው ድርድር በሸኔ አፈንጋጭ ተግባራት መስተጓጎሉ ትልቅ ማሳያ ነዉ ።

Address

Washington D.C., DC

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gadaa Online posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category